#ከምኞት_ባሻገር
የምስኪን አፍቃሪዋ ተግሳፅ..
(በሊዮሪ)
ተመልክቼህ በሸራፋ ቀኔ
ቢሰወረር እኔነቴ
ጀመርኩ
ምኞቴን እየመዘንኩ!!!!!
ላልፈታ ገባው ከፍቅርህ ሉጋም፤
አሰሳዬ እጥግ ደርሶ ብደክም።
እንደ መንገደኛ...
በ'ይታ ሰርጌ ከባህሩ እንብርት፤
አድማስ አልፎ አይኔ አንተ ባትኖርበት።
ቀለሜን አፍስሼ ብሩሹን ሰቀልኩት!!!!!!
እንደ ሰዓሊ...
ዜማ ስደረድር ከቅኔ 'የወጣው
የግጥሜ ድምፀት ጥል ሆኖ__ ቤቴንም ቢያፈርሰው፤
ብኩን እንጉርጉሮዬ አውንታሩን በጠሰው!!!!!!
እንደ አዝማሪ....
ከሌላኛው የነብስ ዋጋ ከሚታፈስበት፤
ሰማይን ዘወትር በአይኖቼ ዳስሴ ከማማትርበት።
አንተ ካለህበት ከስምህ ጉባዬ፤
ልቤ መልስን ሽቶ ከተመ ሱባዬ።
ናፍቆት የከለለው ከፍቅርህ ገዳሜ፤
ልታቀብ ወሰንኩኝ ሲገባኝ ከርሜ።
በዚም...
ደግሞ እንደመናኝ....
ላንተ ካልታደልኩኝ አለም ሙሉ በቃኝ።
በቃኝ!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!
✍ሊዮሪ
21/12/2013ዓ.ም
የሆሄያት ህብር🦋🦋🦋🦋
#የጥበብ_ማዕድ
🦋🦋🦋🦋
@leoyri
@gGetem
@gGetem
>>Click here to continue<<