የዘመነኛው ኑዛዜ!!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።
እንኳን አንተ አባቴ!
ጨለማው ምናብ ላይ ~ ፋኖስን ለኩሰህ
ከመሀል እስከ ጫፍ ~ የዞርከው ጀግነህ
ሀገርን በሌማት.. .
ለመቋደሻችን ~ ዘርግተህ የሰጠህ
ስንቱ ታሪክ አባሽ
ስንቱ አዳም አስለቃሽ
ገሀዱ እውነታው ~ ሀቅታው ታብሎ
ሀውልቱ ይቆማል.. .
ኧኸተማ መሀል ~ ዠግና ነው ተብሎ።
።።።።
እምዬ ሚኒልክ
የፅናታችን ልክ
ሀላፊ አግዳሚው ~ ታሪክህን ቢሰማ
አረሙን መንግሎ...
የባርነትን ጥግ ~ የሀሳቡን ጥሻ ~ መንጥሮ ቢያለማ
ለባንዳ ህመም ሆነህ ~ መቅደሱ ፊትለፊት ~ ቁምልን በግርማ።
።።።።
ቁምልን አባቴ!
በአክሊል አጊጥህ ~ ተውበህ በካባ
ልጓምህን አንቀህ ~ ኸፈረስህ ጀርባ
ማነው? ብለው ሲሉን ~ ንጉስ ነው እንድንል
ሸማችን ሲሳሳ...
ሀገር እንዳይበርዳት ~ ታሪክ እንድንፈትል
ወኔያችን ሲላላ...
ዳግም ዘራፍ ብለን ~ በስምህ እንድንምል
በዓለም ጎዳና ላይ...
ግዞተኛ ሆነን ~ እንዳንቆርጥ ተስፋ
ለምልክት ቆመህ...
የአርነት መለከት ~ በኩራት ይነፋ ።
@leoyri
hottg.com/gGetem
>>Click here to continue<<