እኔ ምልህ?
አገኘሀት?
:
ያቺን ምጥን
የሰው ምታ'ት!
.
ምናለችህ - ስታወጉ ?
ምን ብላለች ~ ስትጫወት ?
ያምና ውድህ ~ ያይንህ ውበት !
.
ትዝ ይላታል ስላለፈው ?
በዛ ቀሚስ ~ ስስ ነፍስህን ስትንጠው?
፡
ትዝ ይላታል ~ ያንተ ሳቅህ ?
ታወሳት ወይ ~ ያ ደረትህ ?
የክንድህ ላይ ~ ንቅሳትህ
ስሟን ያተምክበት
..............ጥቁር ምልክትህ
ትዝ አላት ወይ?
ጥርስ ገላጭ ~ ለዛ ቀልድህ?
፡
ምን ትላለች
ስለ ትናንት —-
ከንፈርህ ዳሳ - ተኩሳህ እንደ እሳት
ልብህን አድብናት…
ቀልብህን አጉናት ...
ስትነጥልህ ፦ ከሰው መንጋ
ለሌላው ጨልመህ ለርሷ ስትነጋ፤
፧
ታወሳት ፦ ትዝ አላት?
.
ተበድረህ ለልደቷ
የአንገት ሀብል ስትገዛላት?
ለብርቋ ቀን ስትደርስላት
.
ውዴ ብላ
ተንጎማላ
ውዱ ብላ
ተገማሽራ
ስትሸጎጥ ስርህ
ተሞልታ ~ በኩራት
ከእናቷ ለጥቆ
በፍቅር ወልደሀት..
ሞገስ ሆነህ
ቅባት ሆነህ
እንደ ጣይቱ አንግሰሀት
ጓዶቿ ፊት ጌጥ ሆነሀት
፡
እንደው ምናለችህ ?
ስታገኛት ፣ ስትቀርባት
ያቺ ምጥን
የሰው ምታ’ት?
.
ምን ብላለች ስትጫወት?
ያምና ውድህ ያይንህ ውበት !
.
ብዬ ብጠይቀው
እየተናነቀው...
.
"ሳቄ አይደል ጠረኔ
ምኑም የላት ከኔ
ይልቅ ስጠይቃት
የታወሳት የገረማት...
ከቀን መርጦ የመጣላት
የኔ ችጋር ~ የኔ ማጣት
ለዓይኗ እንኳ ጠገነንኳት ።"
ብሎ መለሰልኝ...
(ሚካኤል አ)
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨፨፨
፨፨፨፨፨
፨፨፨
፨
@gGetem
@leoyri
>>Click here to continue<<