Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/hottg/post.php on line 59

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/2024-05-22/post/finote_kidusan/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/hottg/post.php on line 72
"ወንጌላዊው ዮሐንስ እመቤታችንን የጠራበት መንገድ" @ፍኖተ ቅዱሳን ꜰɪɴᴏᴛᴇᴋɪᴅᴜsᴀɴ
TG Telegram Group & Channel
ፍኖተ ቅዱሳን ꜰɪɴᴏᴛᴇᴋɪᴅᴜsᴀɴ | United States America (US)
Create: Update:

"ወንጌላዊው ዮሐንስ እመቤታችንን የጠራበት መንገድ"

ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን …………“የኢየሱስ
እናት” ብሎ ጠርቷታል፡፡ ይኼ ሐዋርያ በጻፈው
ወንጌል ላይ የራሱንም ስም እንኳን አንድ ጊዜ
ያልጠራ ትሑት ሰው ቢሆንም የእመቤታችንን
ስም የጠራበት መንገድ እንዲሁ የምናልፈው
አይደለም፡፡ በወንጌሉ/በዮሐንስ ወንጌል/
እመቤታችንን ስምንት ጊዜ አንስቷታል፡፡ /ዮሐ
፪፥፩‚ ፪፥፫‚ ፪፥፭‚ ፪፥፲፪‚ ፮፥፵፪‚ ፲፱፥፳፭
‚ ፲፱፥፳፮‚ ፲፱፥፳፯/ ስምንት ጊዜ ሲጠራት ግን
አንድም ቦታ “ማርያም” ብሎ በስሟ
አልጠራትም፡፡ የጠራት “የኢየሱስ እናት” “እናቱ”
ብቻ ብሎ ነው፡፡ ቅርበት ባይኖረው ነው እንዳንል
ወንጌሉ ድንግል ማርያም በመስቀሉ ሥር
ለዮሐንስ ተሰጥታው “ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ወደ
ቤቱ ወሰዳት” ይላል፡፡ /ዮሐ ፲፱፥፳፯/ ሥጋዋን
መላእክት ነጥቀው ወደ ሰማይ ሲወስዱትም
አብሯት ተነጥቋል፡፡ ይህ ሐዋርያ በወንጌሉ ዐሥራ
አራት ጊዜ ማርያም የሚባሉ ሴቶችን ስም
ቢጽፍም አንድም ጊዜ እመቤታችንን በስሟ
አልጠራትም፡፡
ነገሩን አልን እንጂ እሱማ መጽሐፍ ቅዱስን
ስንመረምር አምላክን ከወለደች ጀምሮ
ከመላእክትም ወገን ሆነ ከሰዎች ወገን እሷን
የጠሩበት መንገድ ሲቀይሩ አይተናል፡፡አምላክን
ከመጸነሷ በፊት “ማርያም ሆይ በእግዚአብሔር
ፊት ጸጋን አግኝተሻልና አትፍሪ” ሲሉ የነበሩት
መላእክት ከወለደች በኋላ ግን “ሕጻኑና እናቱን
ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ” ሲሉ እናገኛለን፡፡ ሉቃ
፩፥፴ ማቴ ፪፥፵፫ አክስቷ ኤልሳቤጥ ልትጠይቅ
በሔደች ጊዜ ኤልሳቤጥ “የጌታ እናት አለች
እንጂ” እንደ ዝምድናዋ “ማርያም” ብላ
አልጠራቻትም፡፡ ሉቃ ፩፥፵፫
ይህ የሆነበት ምክንያት ድንግል ማርያም እጅግ
ታላቅ የክብር ስሟ “እናቱ” “የኢየሱስ እናት”
“የጌታ እናት” “የአምላክ እናት” የሚለው ስለሆነ
ነው፡፡ አንዲት እናት የታወቀ የከበረ ዝነኛ ልጅ
ካላት ለከሟ ይልቅ የእገሌ እናት ተብላ መጠራቷ
የተለመደና ተገቢ ነው፡፡ እመቤታችን ሰማይና
ምድር በእጁ የሠራው የገናናው አምላክ
ለእግዚአብሔር እናቱ ሆናለች፡፡ ስለዚህ ሐዋርያው
በስሟ ከመጥራት ይልቅ በክብር ስሟ “የኢየሱስ
እናት” ብሎ ሊጠራት ወደደ፡፡ ይህን የቅዱስ
ዮሐንስ የመላእክት የቅዱሳኑ ትውፊትና የጉባኤ
ኤፌሶን ውሳኔ ይዘን እኛም ማርያም ከማለት
ይልቅ ወላዲተ አምላክ እመ አምላ እመቤታችን
እመ ብርሃን እንላታለን፡፡

የወላዲተ አምላክ ምልጃዋ ረድኤቷ አይለየን!!

💚 @finote_kidusan 💚
💛 @finote_kidusan 💛
❤️ @finote_kidusan ❤️

"ወንጌላዊው ዮሐንስ እመቤታችንን የጠራበት መንገድ"

ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን …………“የኢየሱስ
እናት” ብሎ ጠርቷታል፡፡ ይኼ ሐዋርያ በጻፈው
ወንጌል ላይ የራሱንም ስም እንኳን አንድ ጊዜ
ያልጠራ ትሑት ሰው ቢሆንም የእመቤታችንን
ስም የጠራበት መንገድ እንዲሁ የምናልፈው
አይደለም፡፡ በወንጌሉ/በዮሐንስ ወንጌል/
እመቤታችንን ስምንት ጊዜ አንስቷታል፡፡ /ዮሐ
፪፥፩‚ ፪፥፫‚ ፪፥፭‚ ፪፥፲፪‚ ፮፥፵፪‚ ፲፱፥፳፭
‚ ፲፱፥፳፮‚ ፲፱፥፳፯/ ስምንት ጊዜ ሲጠራት ግን
አንድም ቦታ “ማርያም” ብሎ በስሟ
አልጠራትም፡፡ የጠራት “የኢየሱስ እናት” “እናቱ”
ብቻ ብሎ ነው፡፡ ቅርበት ባይኖረው ነው እንዳንል
ወንጌሉ ድንግል ማርያም በመስቀሉ ሥር
ለዮሐንስ ተሰጥታው “ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ወደ
ቤቱ ወሰዳት” ይላል፡፡ /ዮሐ ፲፱፥፳፯/ ሥጋዋን
መላእክት ነጥቀው ወደ ሰማይ ሲወስዱትም
አብሯት ተነጥቋል፡፡ ይህ ሐዋርያ በወንጌሉ ዐሥራ
አራት ጊዜ ማርያም የሚባሉ ሴቶችን ስም
ቢጽፍም አንድም ጊዜ እመቤታችንን በስሟ
አልጠራትም፡፡
ነገሩን አልን እንጂ እሱማ መጽሐፍ ቅዱስን
ስንመረምር አምላክን ከወለደች ጀምሮ
ከመላእክትም ወገን ሆነ ከሰዎች ወገን እሷን
የጠሩበት መንገድ ሲቀይሩ አይተናል፡፡አምላክን
ከመጸነሷ በፊት “ማርያም ሆይ በእግዚአብሔር
ፊት ጸጋን አግኝተሻልና አትፍሪ” ሲሉ የነበሩት
መላእክት ከወለደች በኋላ ግን “ሕጻኑና እናቱን
ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ” ሲሉ እናገኛለን፡፡ ሉቃ
፩፥፴ ማቴ ፪፥፵፫ አክስቷ ኤልሳቤጥ ልትጠይቅ
በሔደች ጊዜ ኤልሳቤጥ “የጌታ እናት አለች
እንጂ” እንደ ዝምድናዋ “ማርያም” ብላ
አልጠራቻትም፡፡ ሉቃ ፩፥፵፫
ይህ የሆነበት ምክንያት ድንግል ማርያም እጅግ
ታላቅ የክብር ስሟ “እናቱ” “የኢየሱስ እናት”
“የጌታ እናት” “የአምላክ እናት” የሚለው ስለሆነ
ነው፡፡ አንዲት እናት የታወቀ የከበረ ዝነኛ ልጅ
ካላት ለከሟ ይልቅ የእገሌ እናት ተብላ መጠራቷ
የተለመደና ተገቢ ነው፡፡ እመቤታችን ሰማይና
ምድር በእጁ የሠራው የገናናው አምላክ
ለእግዚአብሔር እናቱ ሆናለች፡፡ ስለዚህ ሐዋርያው
በስሟ ከመጥራት ይልቅ በክብር ስሟ “የኢየሱስ
እናት” ብሎ ሊጠራት ወደደ፡፡ ይህን የቅዱስ
ዮሐንስ የመላእክት የቅዱሳኑ ትውፊትና የጉባኤ
ኤፌሶን ውሳኔ ይዘን እኛም ማርያም ከማለት
ይልቅ ወላዲተ አምላክ እመ አምላ እመቤታችን
እመ ብርሃን እንላታለን፡፡

የወላዲተ አምላክ ምልጃዋ ረድኤቷ አይለየን!!

💚 @finote_kidusan 💚
💛 @finote_kidusan 💛
❤️ @finote_kidusan ❤️


>>Click here to continue<<

ፍኖተ ቅዱሳን ꜰɪɴᴏᴛᴇᴋɪᴅᴜsᴀɴ




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)


Fatal error: Uncaught TypeError: shuffle(): Argument #1 ($array) must be of type array, null given in /var/www/hottg/post.php:344 Stack trace: #0 /var/www/hottg/post.php(344): shuffle() #1 /var/www/hottg/route.php(63): include_once('...') #2 {main} thrown in /var/www/hottg/post.php on line 344