ይህ የሚሆነው ታዲያ ፕሮዲውሰሩ/አምራቹ እና ረዳት ዳይሬክተሩ ሁሉንም የእቅድ እና የቀረፃ መርሃ ግብሮችን የሚፈጽሙበት ጊዜ ነው ማለት ነው፡፡ ብዙውን ጊዜ የቅድመ-ምርት ጊዜዎች በቀረፃ መርሃግብር ላይ በመመስረት ይወሰናሉ። ለምሳሌ ፣ ፊልሙን ለመቅረፅ አንድ ወር የሚወስድ ከሆነ የቅድመ-ምርት/ፕሪ–ፕሮዳክሽን ጊዜ ተመሳሳይ የጊዜ ቆይታ ሊኖረው ይገባል - ያ ማለት ደግሞ አንድ ወር ቅድመ-ምርት ጊዜ ካለ የአንድ ወር የቀረፃ/የምርት ጊዜ ይኖራል ቢኖር ይመከራል ነገርግን ይህ ግድ አይደለም እንደ አምራቹ የአሰራር ሁኔታ አንዳንዴ የቅድመ ምርቱ ጊዜ የሚኖርበት ሁኔታ ይኖራል ፡፡
ቅድመ-ምርት/Pre-Production/ ፣ እንደ የፊልም ሥራው የተለያየ ባህሪ ሊኖረው ይችላል፤ በአጠቃላይ ግን እንደ አንድ የስራ ሂደት ፣ የተወሳሰበ እና በተለይ ከስቱድዬ ውጪ ለሚሰሩ ፕሮዲውሰሮች ወይም ዳይሬክተሮች በሌላው አለም ነፃ ፊልም ሰሪዎች ለሚባሉት ከባድ ሊሆን ይችላል። ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ የተረጋጋ ፣ ፍሬያማ የፊልም ቀረፃን ለማረጋገጥ ከተፈለገ በቅድመ-ምርት ሂደት ውስጥ መካተት ያለባቸውን ከዚህ በታች ያሉ ወደዘጠኝ የሚደርሱ የስራ ሂደቶችን ተከትሎ መስራት ይመከራል፤ እያንዳንዳቸው ሂደቶች የራሳቸውን የሥራ ምድቦች እና የአሰራር ክፍሎች አሏቸው።
>>Click here to continue<<