የፊልም ፕሮዳክሽን 7 የስራ ሂደት ደረጃዎች/The 7 Stages Of Film Production/
1. ማዳበር/ማልማት(Development)
ወደ የፊልም ስራን ማዳበር ደረጃ የሚወስዱን ብዛ ያሉና የተለያዩ መንገዶች አሉ ፡፡ ብዙን ጊዜ ግን ይህ የስራ ሂደት የሚጀምረው ቀደም ሲል በተጻፈ ስክሪፕት ላይ በመነሳት ወይም ደግሞ አስፈፃሚ አምራች/Excutive Producer/ ይዞ በሚነሳው ወደ ስክሪፕትነት የሚለወጥ የፊልም ሃሳብ ላይ በመነሳሳት ነው፤ እንደዚሁም አንድ ፊልምን ለመስራት የተነሳሳ ወይ መደበኛ ስራው የሆነ ፕሮዲውሰር/አምራች በተለያየ መንገድ ያለቀለት የፊልም ድርሰት በማፃፍ ወይም ሃሳቦችን በማፈላለግ መርጦ በመግዛት የሚጀመር ሊሆን ይችላል፡፡ ሌላው መንገድ ደግሞ በአንድ አይነት አላማ ላይ በመመርኮዝ የተፃፈ ወይም የተዘጋጀ ፕሮጀክት - አንድ የፊልም ፕሮዳክሽን ኩባንያ ወደፊልምነት እንዲለውጠው/ እንዲሠራው በሚጠይቅበት ጊዜ ነው ፡፡ በዚያ ጊዜ ታዲያ ፕሮጀክቱን የሚያስጀምረው/የተቀበለው ፕሮዲውሰሩ/አምራቹ ለስራው ሀላፊነት በመውሰድ ስክሪን ጸሐፊውን በመቅጠር በሀሳቡ ላይ መሥራት ይጀምራል ፡፡
የስራ ሂደቱ ከላይ ባነሳናቸው በየትኛውም መንገድ ይጀምር የእድገቱ ሂደት የፊልሙን አጠቃላይ እቅድ እና የስክሪፕት ሃሳብ ያካትታል ፡፡ ጸሐፊዎቹ ሥራቸውን በሚሠሩበት ጊዜ ፕሮዲውሰሩ/አምራቹ ደግሞ ከሽያጩ ሥራ ጀምሮ ገንዘብ የማሰባሰብ ወይም ሀሳቡን እንዲያወጣ የመጀመሪያ ጠቅለል ያለ ቅኝት ያደርጋል ፡፡ ስክሪፕቱ አንዴ ከፀደቀ በኋላ ዳይሬክተሩ ይቀጠርና ከፀሐፊው ጋር በመሆን የፊልም ስራውን ቅኝትን፣ ትረካውን፣ የፊልሙን ሃሳብ በመከለስ ለቀጣይ የስራ ሂደቶች ዝግጁ እንዲሆን ያደርገዋል ማለት ነው።
>>Click here to continue<<