🕊..ሹራ 34..🕊
(ሱመይራ አብዱ)
<<አያቴ ሰው ጎድቶሽ ያውቃል>>
<<በጥቂቱ!!>>
<<ከዛ ምን አደረግሽ?>>
<<ከሰው ምንም መጠበቅ አቆምኩ የኔ ልጅ>>አለችኝ ሙስባሀባውን እየቆጠረች
<<እሱን ካደረግን አንጎዳም?>>
<<እንዴታ የኔ ልጅ ሰው በብዙ ሚጎዳው በብዙ ከሰው ልጅ ሲጠብቅ ነው።ሰው ላይ መመካት ሀረግን ይዞ ለመንጠላጠል መሞከር ነው ሀረግ ምንም አቅም የለውም።በአፀፋው ተበጥሶ መሬት ላይ ይጥልሀል የሰው ልጅም እንደዛው ነው።መመካትህን በጀሊሉ ካደረግክ የሰው ልጅ ነገር እሱ የፈቀደው ቢሆን እንጂ አይነካህም።>>
<<መርሀባ አያቴ>>
<<አላህ ሰው ልብ ላይ ተንጠልጥላ የማትጎዳ የሆነች ልብን ይስጥህ የኔ ልጅ!!>>
👇👇👇
@fezekiru
>>@wezekirsumeyriandhayuna
>>Click here to continue<<