TG Telegram Group & Channel
ጥያቄኽ ምንድነው ሳትሄድ ፈልገው | United States America (US)
Create: Update:

✍️ ኢየሰስ ከድንግል ማርያም ሥጋን አልነሳምን

ክፍል ሰባት
Only jesus የሚባሉት ከድንግል ማርያም ሥጋን አልነሳም ለሚሉት ዛሬን የሚያነሷቸውን ጥቅሶች እናያቸው አለን

" በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል። መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ 53:2)

®ይህ ምዕራፍ ስለ ስለኢየሱስ ክርስቶስ መከራዎች የሚሞትበት መጨረሻ እና ከዚያ አስደናቂ ክንውን ለሰው ልጆች የሚያስገኛቸውን ጥቅሞች ይተነብያል ። እንድሁም ሰው የተሰቃዬውን ኢየሱስን እንዴት እንዴተመለከተው ይገልጻል ፣መሲሑን እንዳልተቀበሉት ይገልጣል።
ገና ከቁጥር አንድ ሲጀምር የሰማንውን ነገር ማን አምኗል ብሎ ይጀምራል። መጽሐፍ እንደሚል
" የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1:11)
ዮሐንስ እንዳለ ኢሳያስም በትንቢቱ እንደተናገረ የመሲሑን መምጣት አላመኑም ነበር አልተቀበሉትም ነበር ኢሳያስም ያሰምንውን ማን አምኗል አለ ጌታ ኢየሱስም እንድህ አለ
" ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ነቢያትን የምትገድል ወደ እርስዋ የተላኩትንም የምትወግር፥ ዶሮ ጫጩቶችዋን ከክንፎችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳችሁምም።"
(የማቴዎስ ወንጌል 23:37) ብሎ ተናገረ።
ከዚያም ኢሳያስ ይቀጥል እና የእግዚአብሔር ክንድ ለማን ተገልጧል ይለናል። እንግድህ ክንድ ለማን ተግልጧል ሲል ክንድ ከሰው ሳይለይ ከመሬት እቃ እንደሚያነሳ ሁሉ ጌታ ኢየሱስም ሰዎችን ከወደቁበት ለማንሳት ከአባቱ ሳይለይ መምጣቱን መናገር ነው። እና ኢሳያስ ለማን ተገልጧል ብሎ ሲናገር ለሰው ልጆችን ለማዳን መምጣቱን የሰው ልጆች ግን ይሄን አለማመናቸውን መናገር ነው። ይቀጥል እና ኢሳያስ እንድህ ይላል በፊቱ እንደቡቃያ ከደረቅ መሬት እንደሥርም አድጓል ይላል ። ከደረቅ መሬት መባሉም ደረቅ መሬት ዘር ቢዘሩበት በቃያ እንደማይስገኘው ሁሉ ሰዎቹም የጌታ መወለድ ቢያድተምሯቸው አይሰሙም ነበር አልተቀበሉትም እንዳለ መጽሐፍ ከላይ እንዳየንው ደረቅ መሬት የተባሉት ሰዎች ናቸው። አድጓል መባሉም በነሱ ዘንድ ትምህርቱ መስፋፋቱን መናገር ነው ።ይቀጥል መልክና ውበት የለውም ባዬንው ግዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም ይላል ይሄን ማለቱም ኢሳያስ ሰዎችን አደ ኢየሱስ ለመሳብ ስንሞክር በሰዎች ዘንድ ደስ የሚያሰኝ የሚማርክ ነገር አላገኘንም ሲል ነው ።እንጅ ምዕራፉ ሰዎች እንዳልተቀበሉት እና እንዴት እንደሚያገላቱት እያወራ ያለአውዱ ከድንግል ሥጋ አለመውሰዱን የሚናገር ነው ማለት የማይሆን ተረት ተረት ነው።ኢሳያስ ይቀጥል እና እንድህ ይለናል " የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ 53:3)
ብሎ መከራን እንደተቀበለ ብዙ ስቃይ እንዳደረሱበት ይናገራል። ባጠቃላይ እሱን እንደናቁት እንዳላከበሩት ሲናገር ከደረቅ መሬት ሲል ተናገረ።

ሌላው only jesus የሚባሉት ከሰው ሥጋን አልነሳም ለማለት የሚያነሱት ጥቅስ ይሄ ነው
" #በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም #በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።"" ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ #ነበረ።"" ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ #አልሆነም።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1:1-3)
" #ቃልም #ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ #አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1:14)

ሌላው እነሱ የሚያነሱት ዮሐንስ ከላይ በመጀመርያ ቃል ነበር ብሎ ቁጥር 14 ያም ቃል ሥጋ ሆነ ስለሚል ሥጋ የሆነው ያ በመጀመሪያ የነበረው ቃል ነው ቃሉ ነው ሥጋ የሆነው ነው እንጅ ሥጋን አልነሳም ነው የሚሉት ።
ግን በመጀመሪያ ቃል ነበር ማለት ምን ማለት ነው ለሚለው ከታች ማብራሪያ አስቀምጥላችሁ አለው
ትንሽ ብቻ እዚህ ጋ ላስቀምጥ እንግድህ ዮሐንስ የቃል ቅድምና መናገሩ ነው አንድን ህፃን ተወለደ ለማለት መጀመሪያ ተፀነሰ ማለት እንደሚገባን ጌታ ቃልም ሰው ከመሆኑ በፊት በቅድምና የነበረ መሆኑን መናገሩ ነው ። ከዚያ ቁጥር 14 ላይ ቃልም ሥጋ ሆነ ብሎ በቅድምና የነበረው ቃል ሰው እንደሆነ ይነግረናል ቃልም ሥጋ ሆነ ማለት ቃልም ሰው ሆነ ማለት ነው ለዚህም ማብራሪያ ከታች አስቀምጥላችሁ አለው ትንሽ ነገር ብቻ ነው እዚህ ጋ የማስቀምጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ስናይ እንድህ የሚል ቃል አለ
" ሥጋ ሁሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል።"
(መዝሙረ ዳዊት 65:2) እንግድህ መዝሙረኛው ዳዊት ሥጋ ሁሉ ሲል ሰው ሁሉ ማለት እንጅ ሥጋ ብቻውን ጸሎት የሚያቀርብ ሁኖ አይደለም ነፍስ የተዋሐደችው ሥጋን ማለቱ እንጅ ዮሐንስም ቃልም ሥጋ ሆነ ሲል ቃልም ሰው ሆነ ማልቱ ነው ። ሌላው ቃልም ሥጋ ሆነ ማለት ቃል ከሥጋ ጋር አንድ ሆነ ማለት ነው በመጽሐፍ ቅዱስ እንድህ የሚል ቃል አለ " ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 2:24) እዚህ ጋ እንግድህ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ ሲል አዳም አዳምነቱን ትቶ ሔዋንም ሔዋንነቷን ትታ ሌላ ሥጋ ይሆናሉ ማለት አይደለም አዳምም አዳምነቱ እንዳለ ሔዋንም ሔዋንነቷ እንዳለ አንድ ይሆናሉ ማለት ነው እንጅ ቃልም ሥጋ ሆነ ሲል ቃልም ሳይለውጥ ቃልነቱን ሳይተው ከሥጋ ጋር አንድ ሆነ ማለት ነው እንድሁም ከእኛ ጋር አንድ ሆነ ማለት ነው እንጅ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚል
" እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 1:23) ይላል እናም ቃልም ሥጋ ሆነ ሲል ቃል ሥጋን ተዋህዶ ከእኛ ጋር እንድ ሆነ ማለት ነው።
ሌላው አሁንም በመጽሐፍ ቅዱስ እንድህ የሚል ቃል አለ " ላባም። በእውነት አንተ አጥንቴ ሥጋዬም ነህ አለው። አንድ ወር የሚያህልም ከእርሱ ጋር ተቀመጠ። "
(ኦሪት ዘፍጥረት 29:14) ሲላው እናይ አለን ያዕቆብን ሥጋዬም ነህ ሲል ከአንድ ሥጋ እንደተካፈሉ መናገሩ ነው እናም ቃልም ሥጋ ሆነ ሲል ሥጋን ገንዘቡ ማድረጉን ሥጋን መንሳቱን መናገር ነው።" ኑ፥ ለእስማኤላውያን እንሽጠው፥ እጃችንን ግን በእርሱ ላይ አንጣል፥ ወንድማችን ሥጋችንም ነውና። ወንድሞቹም የእርሱን ነገር ሰሙት።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 37:27) እንደሚል የእኛን ሥጋ እንደነሳ ለመናገር ነው ሥጋ ሆነ ያለው ጸጋን እና እውነትን ተመልቶ በእኛ አደረ እንድል።
@felgehaggnew
@felgehaggnew
በFacebook ማንበብ ለምትፈልጉ
👇
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=2859730944287555&id=100007520311558
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላድቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር
ይቆየን ይቀጥላል

ጥያቄኽ ምንድነው ሳትሄድ ፈልገው
📃ኢየሱስ ከድንግል ሥጋ አልነሣምን⁉️ *⃣ክፍል ስድስት Only Jesus የሚባሉት ሰዎች ለሚያነሱት ጥያቄ ካቆምንበት እንቀጥላለን " ይልቁንስ ብስብስ የሆነ ሰው፥ " "ትልም የሆነ የሰው ልጅ ምንኛ ያንስ! " (መጽሐፈ ኢዮብ 25:6) ለእነዚህ ሰዎች መጀመሪያ መጠየቅ ያለብን የሰው ልጅ ትል ስለተባለ ኢየሱስ ከድንግል ሥጋ ሊነሳ አይችልም ነው የሚሉት ። እና እነሱ እንድህ ካሉ ኢየሱስ የሰው…
✍️ ኢየሰስ ከድንግል ማርያም ሥጋን አልነሳምን

ክፍል ሰባት
Only jesus የሚባሉት ከድንግል ማርያም ሥጋን አልነሳም ለሚሉት ዛሬን የሚያነሷቸውን ጥቅሶች እናያቸው አለን

" በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል። መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ 53:2)

®ይህ ምዕራፍ ስለ ስለኢየሱስ ክርስቶስ መከራዎች የሚሞትበት መጨረሻ እና ከዚያ አስደናቂ ክንውን ለሰው ልጆች የሚያስገኛቸውን ጥቅሞች ይተነብያል ። እንድሁም ሰው የተሰቃዬውን ኢየሱስን እንዴት እንዴተመለከተው ይገልጻል ፣መሲሑን እንዳልተቀበሉት ይገልጣል።
ገና ከቁጥር አንድ ሲጀምር የሰማንውን ነገር ማን አምኗል ብሎ ይጀምራል። መጽሐፍ እንደሚል
" የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1:11)
ዮሐንስ እንዳለ ኢሳያስም በትንቢቱ እንደተናገረ የመሲሑን መምጣት አላመኑም ነበር አልተቀበሉትም ነበር ኢሳያስም ያሰምንውን ማን አምኗል አለ ጌታ ኢየሱስም እንድህ አለ
" ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ነቢያትን የምትገድል ወደ እርስዋ የተላኩትንም የምትወግር፥ ዶሮ ጫጩቶችዋን ከክንፎችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳችሁምም።"
(የማቴዎስ ወንጌል 23:37) ብሎ ተናገረ።
ከዚያም ኢሳያስ ይቀጥል እና የእግዚአብሔር ክንድ ለማን ተገልጧል ይለናል። እንግድህ ክንድ ለማን ተግልጧል ሲል ክንድ ከሰው ሳይለይ ከመሬት እቃ እንደሚያነሳ ሁሉ ጌታ ኢየሱስም ሰዎችን ከወደቁበት ለማንሳት ከአባቱ ሳይለይ መምጣቱን መናገር ነው። እና ኢሳያስ ለማን ተገልጧል ብሎ ሲናገር ለሰው ልጆችን ለማዳን መምጣቱን የሰው ልጆች ግን ይሄን አለማመናቸውን መናገር ነው። ይቀጥል እና ኢሳያስ እንድህ ይላል በፊቱ እንደቡቃያ ከደረቅ መሬት እንደሥርም አድጓል ይላል ። ከደረቅ መሬት መባሉም ደረቅ መሬት ዘር ቢዘሩበት በቃያ እንደማይስገኘው ሁሉ ሰዎቹም የጌታ መወለድ ቢያድተምሯቸው አይሰሙም ነበር አልተቀበሉትም እንዳለ መጽሐፍ ከላይ እንዳየንው ደረቅ መሬት የተባሉት ሰዎች ናቸው። አድጓል መባሉም በነሱ ዘንድ ትምህርቱ መስፋፋቱን መናገር ነው ።ይቀጥል መልክና ውበት የለውም ባዬንው ግዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም ይላል ይሄን ማለቱም ኢሳያስ ሰዎችን አደ ኢየሱስ ለመሳብ ስንሞክር በሰዎች ዘንድ ደስ የሚያሰኝ የሚማርክ ነገር አላገኘንም ሲል ነው ።እንጅ ምዕራፉ ሰዎች እንዳልተቀበሉት እና እንዴት እንደሚያገላቱት እያወራ ያለአውዱ ከድንግል ሥጋ አለመውሰዱን የሚናገር ነው ማለት የማይሆን ተረት ተረት ነው።ኢሳያስ ይቀጥል እና እንድህ ይለናል " የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ 53:3)
ብሎ መከራን እንደተቀበለ ብዙ ስቃይ እንዳደረሱበት ይናገራል። ባጠቃላይ እሱን እንደናቁት እንዳላከበሩት ሲናገር ከደረቅ መሬት ሲል ተናገረ።

ሌላው only jesus የሚባሉት ከሰው ሥጋን አልነሳም ለማለት የሚያነሱት ጥቅስ ይሄ ነው
" #በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም #በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ።"" ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ #ነበረ።"" ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ #አልሆነም።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1:1-3)
" #ቃልም #ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ #አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1:14)

ሌላው እነሱ የሚያነሱት ዮሐንስ ከላይ በመጀመርያ ቃል ነበር ብሎ ቁጥር 14 ያም ቃል ሥጋ ሆነ ስለሚል ሥጋ የሆነው ያ በመጀመሪያ የነበረው ቃል ነው ቃሉ ነው ሥጋ የሆነው ነው እንጅ ሥጋን አልነሳም ነው የሚሉት ።
ግን በመጀመሪያ ቃል ነበር ማለት ምን ማለት ነው ለሚለው ከታች ማብራሪያ አስቀምጥላችሁ አለው
ትንሽ ብቻ እዚህ ጋ ላስቀምጥ እንግድህ ዮሐንስ የቃል ቅድምና መናገሩ ነው አንድን ህፃን ተወለደ ለማለት መጀመሪያ ተፀነሰ ማለት እንደሚገባን ጌታ ቃልም ሰው ከመሆኑ በፊት በቅድምና የነበረ መሆኑን መናገሩ ነው ። ከዚያ ቁጥር 14 ላይ ቃልም ሥጋ ሆነ ብሎ በቅድምና የነበረው ቃል ሰው እንደሆነ ይነግረናል ቃልም ሥጋ ሆነ ማለት ቃልም ሰው ሆነ ማለት ነው ለዚህም ማብራሪያ ከታች አስቀምጥላችሁ አለው ትንሽ ነገር ብቻ ነው እዚህ ጋ የማስቀምጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ስናይ እንድህ የሚል ቃል አለ
" ሥጋ ሁሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል።"
(መዝሙረ ዳዊት 65:2) እንግድህ መዝሙረኛው ዳዊት ሥጋ ሁሉ ሲል ሰው ሁሉ ማለት እንጅ ሥጋ ብቻውን ጸሎት የሚያቀርብ ሁኖ አይደለም ነፍስ የተዋሐደችው ሥጋን ማለቱ እንጅ ዮሐንስም ቃልም ሥጋ ሆነ ሲል ቃልም ሰው ሆነ ማልቱ ነው ። ሌላው ቃልም ሥጋ ሆነ ማለት ቃል ከሥጋ ጋር አንድ ሆነ ማለት ነው በመጽሐፍ ቅዱስ እንድህ የሚል ቃል አለ " ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 2:24) እዚህ ጋ እንግድህ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ ሲል አዳም አዳምነቱን ትቶ ሔዋንም ሔዋንነቷን ትታ ሌላ ሥጋ ይሆናሉ ማለት አይደለም አዳምም አዳምነቱ እንዳለ ሔዋንም ሔዋንነቷ እንዳለ አንድ ይሆናሉ ማለት ነው እንጅ ቃልም ሥጋ ሆነ ሲል ቃልም ሳይለውጥ ቃልነቱን ሳይተው ከሥጋ ጋር አንድ ሆነ ማለት ነው እንድሁም ከእኛ ጋር አንድ ሆነ ማለት ነው እንጅ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚል
" እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 1:23) ይላል እናም ቃልም ሥጋ ሆነ ሲል ቃል ሥጋን ተዋህዶ ከእኛ ጋር እንድ ሆነ ማለት ነው።
ሌላው አሁንም በመጽሐፍ ቅዱስ እንድህ የሚል ቃል አለ " ላባም። በእውነት አንተ አጥንቴ ሥጋዬም ነህ አለው። አንድ ወር የሚያህልም ከእርሱ ጋር ተቀመጠ። "
(ኦሪት ዘፍጥረት 29:14) ሲላው እናይ አለን ያዕቆብን ሥጋዬም ነህ ሲል ከአንድ ሥጋ እንደተካፈሉ መናገሩ ነው እናም ቃልም ሥጋ ሆነ ሲል ሥጋን ገንዘቡ ማድረጉን ሥጋን መንሳቱን መናገር ነው።" ኑ፥ ለእስማኤላውያን እንሽጠው፥ እጃችንን ግን በእርሱ ላይ አንጣል፥ ወንድማችን ሥጋችንም ነውና። ወንድሞቹም የእርሱን ነገር ሰሙት።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 37:27) እንደሚል የእኛን ሥጋ እንደነሳ ለመናገር ነው ሥጋ ሆነ ያለው ጸጋን እና እውነትን ተመልቶ በእኛ አደረ እንድል።
@felgehaggnew
@felgehaggnew
በFacebook ማንበብ ለምትፈልጉ
👇
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=2859730944287555&id=100007520311558
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላድቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር
ይቆየን ይቀጥላል


>>Click here to continue<<

ጥያቄኽ ምንድነው ሳትሄድ ፈልገው




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)