እንኳን አደራሳችሁ
እግዚአብሔር ከሰው ልጅ የማይተባበሩ ሥስት ልደታትን ተወለደ።እኔም ዐውቄ አደነቅሁ ።ባራተኛው እንጅ የበጎ ዕረፍት አላገኘሁም።
አዳም ከሕቱም ምድር የተወለደ በተፈጥሮ ነው።እኔን ግን የጠቀመኝ የለም ።ሔዋንም ከአዳም ግራ ጎን ተወለደች እርሷም በተፈጥሮ ነው ።ለኔ ግን የጠቀመችኝ የለም።ቃየልም እንደ ሰው ሁሉ በሩካቤ ተወለደ የጠቀመኝ የረባኝ የለም ። ስንኳን እኔን እራሱንም አልጠቀመም ።እሊህ ሦስቱ ልደታትም ለማንም ለማን አይረቡም አይጠቅሙም።ክርስቶስ ግን ያለዘር ያለሩካቤ ከድንግል ተወለድ የሚረባ የሚጠቅም ሆነ።ለዚህ ልደት መስገድ መገዛት ይገባል።ክብር ምስጋና ለዚህ ልደት ይገባል ጌትነትና ገናንነት ኅያልነት፣አዚዝነት፣እልልታ፣ግርግታ ለዚህ ልደት ይገባል።ይህ ጥበብ ፍልስፍና እጡብ ድንቅ ነው።ለዚህ አንክሮ ይገባል ይህም የሥጋዊ ምሥጥር ምን ይርቅ ምን ይጠልቅ።ለዚህ አንክሮ ይገባል።ይህም ሰው መሆን ሥጋ መልበስ እጅግ እጹብ ድንቅ ነው።
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
@felgehaggnew
@felgehaggnew
>>Click here to continue<<