ይኸውልሽ...
"""""""""""
ከዘመን አትኳረፊ የጊዜ በትር አይንካሽ
በሰው ፊት የሚያሸማቅቅ
አጊንቶ ማጣት አይጎብኝሽ።
የዕድሜሽ ቀንበጥ ዛላ ያፍራ
ውበትሽ ያብብ ይጎምራ።
እንጂማ...
የሆንሽ እንደሁ የቀን ሲሳይ
ከተጠፈርሽ በቀን ግዳይ፤
ምስጢርሽ ገሃድ ከወጣ
ገበናሽ ፀሐይ ከሞቀው፥
ወድቀሽ የተገኘሽ 'ለት
የሚፈርድብሽ ብዙ ነው።
አረጋኸኝ መንገሻ(ፋና ብዕር)
>>Click here to continue<<