TG Telegram Group & Channel
ህብረ ቀለማት ግጥሞች | United States America (US)
Create: Update:

የማስተጋባት ክፉ ደዌ
.
ደብረ ሊባኖሳዊው ባለ ቅኔ ካህሊል ጅብራን እንዲህ ይላል:-"አንዱ ሰው በውስጡ ሁለት ሰዎችን ነው፤አንዱ በብርሃን ሲተኛ ሌላው በጨለማ ይነቃል" ይላል ይህቺን ይዘን ሌላ ከፈለጋችን እንጭለፍ። ሳንሞቀው የጠለቀው ፀሀያች አያ ሙሌ ሙሉ -ጌታ ተስፋዬ(አያዬ) ደግሞ " ለካ ሰው ጥንድ ነው የአንድ ራስ መንትያ
አንድ ነው ሲካፈል" ይለናል እያወዳደርኩ አይደለም። ግን ቢያንስ ያለንን እንወቅ። ማንም ማንንም አልቀደመም አልበለጠምም ራሱን እስካልቀደመ በቀር።ነገ ስም ያለው ተነስቶ ስለ አያ ሙሌ ቢያወራ አሽቃብጠን እና አለ ልክ አውርተን ዝም ነን። አድናቂ ከማድነቁ በፊት የሚያደንቀውን ሰው እና ግብሩን ቢያንስ በአረዳዳችን መጠን እንኳን እንወቀው ግድ የለም ጥበብ መንጋነት አትደግፍም። የሚገርመው ግን የሀገራችን የስነ ፅሁፍ አለም በመንጋ የሀሳብ ዳራ ተተብትቧል።አንድ ጫፍ ይዞ ስለ አንድ ሰው ብቻ መለፈፍ ታሪክ ገደላ ነው።
ምን አይነት የዘመኑ ዘዴ አለ መሰላችሁ የባዕድ ቋንቋ በንግግር መሃል መደብለቅ የአዋቂነት ልክ እንደሆነው ሁሉ በስነ ፅሁፍ ችሎታቸው ገዘፍ ያሉትን ስም እየጠቀሱ ገሳ መጠለል ደግሞ አዋቂነት ሆኗል።እኔ ግን አይመስለኝም። ቀድሞ ነገር የገባን ራሱ አልገባንም።የጥበብ ሰው ደግሞ ጣዎስ ወይም ኮፒ ማሽን አይደለም ከሌላው የሰማውን ለማሰማት በስማ በለው አይጋልብም።ኢትዮጵያዬ ሆይ ጥበበኞችን ስንጠራ ብቅ የሚሉትን አንድ በይልኝ እኛ ጥበበኞችን እንጂ የቡና ወረኞችን አልጠራንም።ለማንኛውም ይህን ያልኩት በማያቸው መደጋገሞች ነው። ስጋ ቤት ሲከፈት መደዳውን ስጋ ቤት መክፈት ንግድ ነው። ስጋ ቤት ሲከፈት ከጎኑ እንጀራ ቤት ፣ ቢላ መሞረጃ ቤት እና የመሳሰሉትን መክፈት ደግሞ ጥበብ ነው።
በረሃ ላይ ውሃ ፍለጋ አንዲት ቦታ ላይ ቆፍረህ ውሃ ስታገኝ ኩባያ ይዞ ከሚመጣው ሰው ይልቅ የተገኘውን ምንጭ ደግሞ ለመቆፈር የሚመጣው ይበዛል። የገጠመን ይህ ነው። ወይ ለመጠጣት ኩባያ ይዘህ ና ወይም ፈቅ ብለህ ቆፍር። ብዙዎቻችን ሰው ከሚተቸን ተኩሶ ቢገድለን እንመርጣለን እና በማወቅም ባለማወቅም የተቀየመ ካለ ይቅር ይበለኝ። እኔም ይቅርታን ጠይቄያለሁ። ቸር ሰንብቱማ
ያለንን እንወቅ!!
አድናቂነት በግርድፉ ሳይሆን ሰርፆ ይግባን!!
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
©ሲራክ
@ethiopiagna
@ethiopiagna

የማስተጋባት ክፉ ደዌ
.
ደብረ ሊባኖሳዊው ባለ ቅኔ ካህሊል ጅብራን እንዲህ ይላል:-"አንዱ ሰው በውስጡ ሁለት ሰዎችን ነው፤አንዱ በብርሃን ሲተኛ ሌላው በጨለማ ይነቃል" ይላል ይህቺን ይዘን ሌላ ከፈለጋችን እንጭለፍ። ሳንሞቀው የጠለቀው ፀሀያች አያ ሙሌ ሙሉ -ጌታ ተስፋዬ(አያዬ) ደግሞ " ለካ ሰው ጥንድ ነው የአንድ ራስ መንትያ
አንድ ነው ሲካፈል" ይለናል እያወዳደርኩ አይደለም። ግን ቢያንስ ያለንን እንወቅ። ማንም ማንንም አልቀደመም አልበለጠምም ራሱን እስካልቀደመ በቀር።ነገ ስም ያለው ተነስቶ ስለ አያ ሙሌ ቢያወራ አሽቃብጠን እና አለ ልክ አውርተን ዝም ነን። አድናቂ ከማድነቁ በፊት የሚያደንቀውን ሰው እና ግብሩን ቢያንስ በአረዳዳችን መጠን እንኳን እንወቀው ግድ የለም ጥበብ መንጋነት አትደግፍም። የሚገርመው ግን የሀገራችን የስነ ፅሁፍ አለም በመንጋ የሀሳብ ዳራ ተተብትቧል።አንድ ጫፍ ይዞ ስለ አንድ ሰው ብቻ መለፈፍ ታሪክ ገደላ ነው።
ምን አይነት የዘመኑ ዘዴ አለ መሰላችሁ የባዕድ ቋንቋ በንግግር መሃል መደብለቅ የአዋቂነት ልክ እንደሆነው ሁሉ በስነ ፅሁፍ ችሎታቸው ገዘፍ ያሉትን ስም እየጠቀሱ ገሳ መጠለል ደግሞ አዋቂነት ሆኗል።እኔ ግን አይመስለኝም። ቀድሞ ነገር የገባን ራሱ አልገባንም።የጥበብ ሰው ደግሞ ጣዎስ ወይም ኮፒ ማሽን አይደለም ከሌላው የሰማውን ለማሰማት በስማ በለው አይጋልብም።ኢትዮጵያዬ ሆይ ጥበበኞችን ስንጠራ ብቅ የሚሉትን አንድ በይልኝ እኛ ጥበበኞችን እንጂ የቡና ወረኞችን አልጠራንም።ለማንኛውም ይህን ያልኩት በማያቸው መደጋገሞች ነው። ስጋ ቤት ሲከፈት መደዳውን ስጋ ቤት መክፈት ንግድ ነው። ስጋ ቤት ሲከፈት ከጎኑ እንጀራ ቤት ፣ ቢላ መሞረጃ ቤት እና የመሳሰሉትን መክፈት ደግሞ ጥበብ ነው።
በረሃ ላይ ውሃ ፍለጋ አንዲት ቦታ ላይ ቆፍረህ ውሃ ስታገኝ ኩባያ ይዞ ከሚመጣው ሰው ይልቅ የተገኘውን ምንጭ ደግሞ ለመቆፈር የሚመጣው ይበዛል። የገጠመን ይህ ነው። ወይ ለመጠጣት ኩባያ ይዘህ ና ወይም ፈቅ ብለህ ቆፍር። ብዙዎቻችን ሰው ከሚተቸን ተኩሶ ቢገድለን እንመርጣለን እና በማወቅም ባለማወቅም የተቀየመ ካለ ይቅር ይበለኝ። እኔም ይቅርታን ጠይቄያለሁ። ቸር ሰንብቱማ
ያለንን እንወቅ!!
አድናቂነት በግርድፉ ሳይሆን ሰርፆ ይግባን!!
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
©ሲራክ
@ethiopiagna
@ethiopiagna


>>Click here to continue<<

ህብረ ቀለማት ግጥሞች




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)