የሱፍ አበባ "
ከሚለው መጽሐፍ የተቆነጠሩ ገፆች...
"ጎበዝ ሰው ለጥያቄዎች በሚሰጠው መልስ ይታወቃል። ብልህ ሰው ግን በሚጠይቀው ጥያቄ ይመዘናል።"
/ የሱፍ አበባ...ገጽ 56 /
"ድርቅ የተፈጥሮ ምክንያት አለው። ርሀብ ግን ሁሌም የተዛባ ፖለቲካዊ መስመርና ፖሊሲ ውጤት ነው። "
/ የሱፍ አበባ...ገጽ 66 /
"...ሞኝ አትሁን! ፍቅር፣ ወሲብ፣ ምናምን ቀድሞ የተዘጋጀ ቀመር የለውም። የምክንያትና የሎጂክ ጣጣም አያውቅ። ድንገት ብቅ ይላል፣ ሀሴት አዝንቦልህ መልሶ ይሰወራል። እንደገና ትናፍቀዋለህ። ይሄንን የተፈጥሮ ሕግ እንኳንስ አንተ የፍቅር አማልክት ሊለውጡት አይችሉም ።..."
/ የሱፍ አበባ...ገጽ 119 /
"ምሥጢር በትክክል ምሥጢር የሚሆነው የአንተ እስረኛ ሲሆን ነው። ሌላ ሰው ጆሮ ከደረሰ ግን አንተ የምሥጢርህ እስረኛ ትሆናለህ!..."
/ የሱፍ አበባ...ገጽ 128 /
"የሚኖሩለት ዓላማ አለ ማለት ከእንስሳዊ ተፈጥሮ እየወጡ...እየራቁ...አየመጠቁ መሄድ ማለት ነው ። "
/ የሱፍ አበባ...ገጽ 131 /
#share
@ethiopiagna
@ethiopiagna11
>>Click here to continue<<