ዐርብ፡- ቤተ ክርስቲያን
በክርስቶስ ደም ተዋጅታ ለተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታላቅ መታሰቢያ በመሆኗ በሰሙነ ፋሲካው ያለችው ዐርብ ቤተ ክርስቲያን ተብላ ትጠራለች፡፡ ማቴ.26-26-29, የሐ. ሥራ. 20-28
ይህች ዕለት ሦስት ስያሜዎች አሏት፡፡ ይኸውም፡-
1.ተጽዒኖ፡- አንደኛው ከሆሳዕና ቅዳሜ በፊት ያለችው ዐርብ የጌታችን ጾም የሚፈጸምባት፤ የጾመ ድጓው ቁመትም የሚያበቃባት፣ በመሆኗ በቤተ ክርስተያን ተጽዒኖ ስትባል፤ በሕዝቡም ዘንድ በሕማማትና ሰሙነ ትንሣኤው ከባዱን ሥራ ስለሚያቆምባት የወፍጮ መድፊያ፣ የቀንበር መስቀያ ትባላለች፡፡
2.አማናዊቷ ዐርብ፡- ሁለተኛውም በመጀመሪያ የሰው አባትና እናት አዳምና ሔዋን ስለተፈጠሩባት፣ ኋላም በሐዲስ ኪዳን ጌታችን ለቤዛ ዓለም መከራ ተቀብሎ ስለተሰቀለባትና የማዳን ሥራውን ስለፈጸመባት ዕለተ ስቅለት አማናዊቷ ዐርብ ትባላለች፡፡
3.ቤተ ክርስቲያን፡- ሦስተኛው በሰሙነ ትንሣኤው ያለችው ደግሞ ቤተ ክርስቲያን ትባላለች ማለት ነው፡፡
@ethioadbrat
>>Click here to continue<<