TG Telegram Group & Channel
+ ቅዱስ እስጢፋኖስ | 𝚂𝚝 𝚂𝚝𝚎𝚙𝚑𝚎𝚗 + | United States America (US)
Create: Update:

የሐዲስ ኪዳን ወንጌል ጸሓፊያን ግን ‹‹ረጅም ተራራ፣ ቅዱስ ተራራ›› በማለት ጠርተውታል፡፡ ሆኖም ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ተራራ ላይ ክብሩን እንደገለጠና የዚህም ተራራ ስም ታቦር መሆኑን ሐዋርያት በሲኖዶሳቸው ገልጠዋል፣ በትውፊትም ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድም ይህንን ረጅም ተራራ ደብረ ታቦር እያለ በድጓው አስፍሮታል፡፡

በዚህ በዓል አምላክነት፣ ጌትነት፣ ንግሥና የባሕርይ ገንዘቡ መሆኑን፣ የድኅነታችን መሠረቱም የጌታችን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው መሆን (የተዋሕዶ ምሥጢርን)  የገለጸበት በዓል ነው፡፡ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ “እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም ወገብረ መድኃኒተ በማእከለ ምድር/ እግዚአብሔር ግን ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፣ በምድርም መካከል መድኀኒትን አደረገ” (መዝ.፸፪፡፲፪) በማለት ትንቢት የተናገረው ለዚህ ነው፡፡ ማእከለ ምድር በተባለች በቀራንዮ ሰው የሆነ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ቤዛነት ዓለሙን ሁሉ አድኗልና፡፡ ሆኖም ግን የጌታችን ነገረ ተዋሕዶ ምሥጢር በሥጋዊ ዕይታ ውስጥ ለሆኑት ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኖባቸዋል፡፡

ብርሃነ መለኮቱ የተገለጠበት  ምሥጢር፡-

ሦስቱ ሐዋርያት በተራራው ሳሉ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መልኩ በፊታቸው ተለወጠ፡፡ ይህ የብርሃነ መለኮቱ የመገለጥ የተዋሕዶ ምሥጢር እንጂ ውላጤ/መለወጥ/ አይደለም፡፡ “እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም” እንዲል፡፡(ሚል ፫፥፮)፡፡ ሦስት ክንድ ከስንዝር አካል ምሉዕ ብርሃን ሆኗል፡፡ ፊቱም እንደ ፀሐይ ብሩህ ሆነ፡፡ ልብሱም እንደ በረድ ጸዓዳ ሆነ፡፡ ይህ ሁሉ ነገረ ተዋሕዶን እንዲረዱ የተደረገ የተዋሕዶ ምሥጢር ነው፡፡ ሰውነቱን ባይክዱም አምላክነቱን ግን ተጠራጥረው ስለነበር እነር በሚያውቁት በባሕርየ ትስብዕቱ አምላክነቱን ከሰውነቱ አዋሕዶ ምሥጠረ ተዋሕዶን ገለጠላቸው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ በ፴፪ ዓመት ከ፮ ወር ከ፲፫ ቀን፣ በዘመነ ማቴዎስ፣ በወርኃ ነሐሴ በዕለተ እሑድ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን ገልጧል፡፡

ሙሴንና ኤልያስን በደብረ ታቦር ለምን አመጣቸው?

ሙሴን ከመቃብር ጠርቶ ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን ወደ ደብረ ታቦር እንዲመጡ ያደረገበት ምክንያት ጌታችን አምለካችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ መሆኑን እንዲመሰክሩ ነው፡፡ ሙሴ ከመቃብር ተነሥቶ ስለጌታችን የሰጠው ምስክርነት፡- “እኔ ባሕር ብከፍልም፣ውኃ ከዓለት ላይ ባፈልቅም፣ በዓመደ ደመና ዕብራውያንን እየመራሁ ጠላትን ድል ባደርግም፣ ደመና ብጋርድም፣መና ከደመና ባወርድም በአንተ መልካም ፈቃድ ነው፤ ብዙ ተአምራንት እንዳደርግ የረዳኝን የእኔን ፈጣሪ እንዴት ሙሴ ነው ይሉሃል? የሙሴ አምላክ እግዚአብሔር ይበሉህ እንጂ!” ሲል ኤልያስም ደግሞ “እኔ ሰማይ ዝናብ እንዳይሰጥ ብለጉም፣ እሳት ባዘንብም፣ እስራኤልን ከክፋታቸው ማዳን የማይቻለን ነኝ እንዴት የእኔን ፈጣሪ ኤልያስ ነህ ይሉሃል? የኤልያስ ፈጣሪ እግዚአብሔር ይበሉህ እንጂ!” በማለት የባሕርይ አምላክነቱን በደብረ ታቦር ላይ መስክረዋል፡፡ ሙሴና ኤልያስ የተጠሩበት ሌላው ምሥጢር ሙሴ “ጀርባዬን ታያለህ፤ ፊቴን ግን አይታይም” ተብሎ ስለነበር (ዘፀ.፴፫፡፳፫) ከሞትም ከብዙ ዘመናት በኋላ ተነሥቶ ጌታን በአካል የማየትና ምስክርንት የመስጠት የቃል ኪዳን ተስፋ መፈጸሙን፣ ኤልያስም “በኋለኛው ዘመን ምስክሬ ትሆናለህ” ስለተባለ ያንን ለመፈጸም ሲሆን ካገቡት ሙሴን ከደናግል ኤልያስን ያመጣቸው መንግሥተ ሰማያት በሕግ የተጋቡ ሕጋውያንና ሥርዐት ጠብቀው የሚኖሩ ደናግላን እንደሚወርሷት ለማስተማር ሁለቱን ወደ ድበረ ታቦር አምጥቷቸዋል፡፡

መድኃኒታችን ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን “መነይብልዎ ሰብእ ለወልደ እጓለ እምሕያው፤ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል? ብሎ ጥየቋቸው ነበርመና ሲመልሱ አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ›› ብለውት ነበርና (ማቴ.፲፮፡፲፬)፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ‹‹በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር›› ያለውም የነበራቸውን ክብር ታላቅነት ያስረዳል፡፡

በባሕርዬ አይተህ ደንግጠህ እንዳትሞት በብርሃን ሠረገላ ሆኜ እስካልፍ ድረስ ቀዳዳ ባለው ዋሻ እሠውርሃለሁ፡፡ በብርሃን ሠረገላ ሆኜ ካለፍሁ በኋላ እጄን አንሥቼልህ ከወደ ኋላዬ ታየኛለህ እንጂ በባሕርዬ ግን ፊቴን ማየት አይቻልህም›› የሚል ምላሽ ሰጥቶት ነበር (ዘፀ. ፴፫፡፲፫-፳፫)፡፡ ይህም በፊት የሚሄድ ሰው ኋላው እንጂ ፊቱ እንደማይታይ ጌታም በባሕርዩ አለመገለጡን ያስረዳል፡፡ ምሥጢሩም አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም አምላክ ሰው ሆኖ ሥጋን ተዋሕዶ በደብረ ታቦር በባሕርዩ እስኪገለጥለት ድረስ ሙሴ በመቃብር ተወስኖ እንደሚቆይ ያጠይቃል፡፡ በእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ከሙታን ተነሥቶ ከዘመናት በፊት የተመኘውን የአምላኩን ፊት ለማየት የታደለው ሊቀ ነቢያት ሙሴ የተወለደውም በዚህች ዕለት ነው፡፡ ነቢዩ ኤልያስም “በኋለኛው ዘመን ምስክሬ ትሆናለህ” የተባለው ትንቢትም በዚህች ዕለት ተፈጸመ፡፡

ይቀጥላል...

የሐዲስ ኪዳን ወንጌል ጸሓፊያን ግን ‹‹ረጅም ተራራ፣ ቅዱስ ተራራ›› በማለት ጠርተውታል፡፡ ሆኖም ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ተራራ ላይ ክብሩን እንደገለጠና የዚህም ተራራ ስም ታቦር መሆኑን ሐዋርያት በሲኖዶሳቸው ገልጠዋል፣ በትውፊትም ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድም ይህንን ረጅም ተራራ ደብረ ታቦር እያለ በድጓው አስፍሮታል፡፡

በዚህ በዓል አምላክነት፣ ጌትነት፣ ንግሥና የባሕርይ ገንዘቡ መሆኑን፣ የድኅነታችን መሠረቱም የጌታችን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው መሆን (የተዋሕዶ ምሥጢርን)  የገለጸበት በዓል ነው፡፡ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ “እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም ወገብረ መድኃኒተ በማእከለ ምድር/ እግዚአብሔር ግን ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፣ በምድርም መካከል መድኀኒትን አደረገ” (መዝ.፸፪፡፲፪) በማለት ትንቢት የተናገረው ለዚህ ነው፡፡ ማእከለ ምድር በተባለች በቀራንዮ ሰው የሆነ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ቤዛነት ዓለሙን ሁሉ አድኗልና፡፡ ሆኖም ግን የጌታችን ነገረ ተዋሕዶ ምሥጢር በሥጋዊ ዕይታ ውስጥ ለሆኑት ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኖባቸዋል፡፡

ብርሃነ መለኮቱ የተገለጠበት  ምሥጢር፡-

ሦስቱ ሐዋርያት በተራራው ሳሉ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መልኩ በፊታቸው ተለወጠ፡፡ ይህ የብርሃነ መለኮቱ የመገለጥ የተዋሕዶ ምሥጢር እንጂ ውላጤ/መለወጥ/ አይደለም፡፡ “እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም” እንዲል፡፡(ሚል ፫፥፮)፡፡ ሦስት ክንድ ከስንዝር አካል ምሉዕ ብርሃን ሆኗል፡፡ ፊቱም እንደ ፀሐይ ብሩህ ሆነ፡፡ ልብሱም እንደ በረድ ጸዓዳ ሆነ፡፡ ይህ ሁሉ ነገረ ተዋሕዶን እንዲረዱ የተደረገ የተዋሕዶ ምሥጢር ነው፡፡ ሰውነቱን ባይክዱም አምላክነቱን ግን ተጠራጥረው ስለነበር እነር በሚያውቁት በባሕርየ ትስብዕቱ አምላክነቱን ከሰውነቱ አዋሕዶ ምሥጠረ ተዋሕዶን ገለጠላቸው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ በ፴፪ ዓመት ከ፮ ወር ከ፲፫ ቀን፣ በዘመነ ማቴዎስ፣ በወርኃ ነሐሴ በዕለተ እሑድ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን ገልጧል፡፡

ሙሴንና ኤልያስን በደብረ ታቦር ለምን አመጣቸው?

ሙሴን ከመቃብር ጠርቶ ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን ወደ ደብረ ታቦር እንዲመጡ ያደረገበት ምክንያት ጌታችን አምለካችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ መሆኑን እንዲመሰክሩ ነው፡፡ ሙሴ ከመቃብር ተነሥቶ ስለጌታችን የሰጠው ምስክርነት፡- “እኔ ባሕር ብከፍልም፣ውኃ ከዓለት ላይ ባፈልቅም፣ በዓመደ ደመና ዕብራውያንን እየመራሁ ጠላትን ድል ባደርግም፣ ደመና ብጋርድም፣መና ከደመና ባወርድም በአንተ መልካም ፈቃድ ነው፤ ብዙ ተአምራንት እንዳደርግ የረዳኝን የእኔን ፈጣሪ እንዴት ሙሴ ነው ይሉሃል? የሙሴ አምላክ እግዚአብሔር ይበሉህ እንጂ!” ሲል ኤልያስም ደግሞ “እኔ ሰማይ ዝናብ እንዳይሰጥ ብለጉም፣ እሳት ባዘንብም፣ እስራኤልን ከክፋታቸው ማዳን የማይቻለን ነኝ እንዴት የእኔን ፈጣሪ ኤልያስ ነህ ይሉሃል? የኤልያስ ፈጣሪ እግዚአብሔር ይበሉህ እንጂ!” በማለት የባሕርይ አምላክነቱን በደብረ ታቦር ላይ መስክረዋል፡፡ ሙሴና ኤልያስ የተጠሩበት ሌላው ምሥጢር ሙሴ “ጀርባዬን ታያለህ፤ ፊቴን ግን አይታይም” ተብሎ ስለነበር (ዘፀ.፴፫፡፳፫) ከሞትም ከብዙ ዘመናት በኋላ ተነሥቶ ጌታን በአካል የማየትና ምስክርንት የመስጠት የቃል ኪዳን ተስፋ መፈጸሙን፣ ኤልያስም “በኋለኛው ዘመን ምስክሬ ትሆናለህ” ስለተባለ ያንን ለመፈጸም ሲሆን ካገቡት ሙሴን ከደናግል ኤልያስን ያመጣቸው መንግሥተ ሰማያት በሕግ የተጋቡ ሕጋውያንና ሥርዐት ጠብቀው የሚኖሩ ደናግላን እንደሚወርሷት ለማስተማር ሁለቱን ወደ ድበረ ታቦር አምጥቷቸዋል፡፡

መድኃኒታችን ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን “መነይብልዎ ሰብእ ለወልደ እጓለ እምሕያው፤ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል? ብሎ ጥየቋቸው ነበርመና ሲመልሱ አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ›› ብለውት ነበርና (ማቴ.፲፮፡፲፬)፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ‹‹በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር›› ያለውም የነበራቸውን ክብር ታላቅነት ያስረዳል፡፡

በባሕርዬ አይተህ ደንግጠህ እንዳትሞት በብርሃን ሠረገላ ሆኜ እስካልፍ ድረስ ቀዳዳ ባለው ዋሻ እሠውርሃለሁ፡፡ በብርሃን ሠረገላ ሆኜ ካለፍሁ በኋላ እጄን አንሥቼልህ ከወደ ኋላዬ ታየኛለህ እንጂ በባሕርዬ ግን ፊቴን ማየት አይቻልህም›› የሚል ምላሽ ሰጥቶት ነበር (ዘፀ. ፴፫፡፲፫-፳፫)፡፡ ይህም በፊት የሚሄድ ሰው ኋላው እንጂ ፊቱ እንደማይታይ ጌታም በባሕርዩ አለመገለጡን ያስረዳል፡፡ ምሥጢሩም አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም አምላክ ሰው ሆኖ ሥጋን ተዋሕዶ በደብረ ታቦር በባሕርዩ እስኪገለጥለት ድረስ ሙሴ በመቃብር ተወስኖ እንደሚቆይ ያጠይቃል፡፡ በእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ከሙታን ተነሥቶ ከዘመናት በፊት የተመኘውን የአምላኩን ፊት ለማየት የታደለው ሊቀ ነቢያት ሙሴ የተወለደውም በዚህች ዕለት ነው፡፡ ነቢዩ ኤልያስም “በኋለኛው ዘመን ምስክሬ ትሆናለህ” የተባለው ትንቢትም በዚህች ዕለት ተፈጸመ፡፡

ይቀጥላል...


>>Click here to continue<<

+ ቅዱስ እስጢፋኖስ | 𝚂𝚝 𝚂𝚝𝚎𝚙𝚑𝚎𝚗 +




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)