ንጉሰ ሰላም🌿
ጨርሰህ የምትጀምር ፣ ቃለ ሕይወትን የምትሰጥ የቃል መፍለቂያ ፣ ንጉሰ ሰላም ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አመሰግንሃለሁ ። ደብረዘይትና ቤተ ፋጌ እንደሚቀራረቡ ልቤን ወደ ቃላህ አቅርብልኝ ። ከመንደር ውስጥ የምትገለገልባቸውን አህያና ውርጫይቱን እንዳገኘ የልቤን መንደር ፈትሸውና አረሙን አቃጥልልኝ። አህያና ውርጫይቱ ላይ መቀመጥህ ተአምር ነው ደንቆኛል ! እኩል የሆኑ አህዮች ላይ መቀመጥ በራሱ ከባድ ነው ፤ አንተ ግን ውርጫይቱ ላይ ተቀመጥከ ። አንዷ ትንሽ ናት አንዷ ከፍ ያለች ናት ። አንዷ ልምጥ ነች አንዷ ደልዳላ ነች አንተ ግን በተአምራት ሁለቱም ላይ ተቀመጥክባቸው። ምግባሬ ትንሽ ትዕቢቴ ብዙ ፣ ለትዕዛዝህ ልምጥ ለኃጢአት ብርቱ የሆንኩ ነኝ ። ሚገድብህ ድንበር የሌለ ንጉሰ ሰላም ክርስቶስ ሆይ የማልመቸውን ልጅህን ስራኝ ። በእስራኤላውያን ልማድ ሀገር ላይ ጦርነት ሲኖር ንጉሱ በፈረስ ላይ ጦር ይዞ በመንደር ውስጥ ይመላለሳል። ሀገሪቱ ሰላም ከሆነች በአህያ ላይ ተቀምጦ መንደሩን በሙሉ እንደሚመላለሳል አንተ ንጉሰ ሰላም ነህና ውርጫይቱ ላይ ተቀምጠህ ወደ ከተማው ገባህ፤ ጌታዬ ሆይ ሀገሬ ኢትዮጵያ አትገባም ወይ ? ወደ ታወከው ልቤስ አትገባም ወይ? የኔ ጌታ ቀርበህ ለከተማይቱ አዘንክ አይደል! ኢትዮጵያን ስትቀርባት ስንቴ አዝነህ ይሆን? የሰላም ንጉሷን አንተን ገፍታ መሳሪያን ስትደገፍ ለኢትዮጵያ አታዝንም ወይ ? አንተን አምላክ ብሎ ሌላ ለሚሚመኘው ልቤስ ስንቴ አዝነህ ይሆን ? ንጉሰ ሰላመቸውን ትተው የዓለማዊያንን ዕቅድ ለሚያራምዱ አገልጋዮች እንዴት አዝነህ ይሆን? ብቻ ሆሳዕና በአርያም ለአንተ ይሁን።ስባዝን በሚሰበስበኝ ፍቅርህ ፣ ስደክም በሚያበረታኝ ድምፅህ ፣ ስታሰር በሚፈታኝ ቃልህ ለዘለዓለሙ አሜን !
#share
#share
ዲያቆን እስጢፋኖስ ደጀኔ🌿
ሚያዚያ 20 ቀን 2016 ዓ.ም.
▫️@diyakonhenokhaile 🌿
https://hottg.com/diyakonhenokhaile
>>Click here to continue<<