" መንገደኛ የተሰኘውን መጽሐፍ አንብቤ ተደንቄአለሁ፡፡ መጽሐፉ የጥልቅ ጥናት ውጤት ከመሆኑ ባሻገር በተዋበ ግልፅ ቋንቋ የቀረበ እጅግ አስፈላጊ ስራ ነው፡፡ ወደ ደቡብ አፍሪካ ስለሚሰደዱ ሰዎች የደቡብ አፍሪካ ዜጋ ያልሆነ ሰው ምርምርና ጥናት አድርጎ ሲያቀርብ ይህ የመጀመሪያ ነው፡፡ መጽሐፉ የስደተኞቹን ቅድመ-ስደት ሕይወት ይዳስሳል፤ ከደቡብ አፍሪካ ደርሰው የሚጋፈጧቸውን የኑሮ ተግዳሮቶችም ወለል አድርጎ ያሳያል፡፡ ከዚያም አልፎ የደቡባዊ አፍሪካ አገሮችን የፖለቲካና ማሕበራዊ ጭብጦችን ይነካካል፡፡ ወደፊት የስደት ጉዳይን በተመለከተ ሊደረግ የሚገባውን የጥናት አቅጣጫም ይጠቁማል፡፡ "
ዶክተር ጌታቸው ተድላ፤ የገጠር ልማት ባለሙያና ደራሲ
>>Click here to continue<<