"እድሜ መገስገሱን ከንቱ ሰው ዘንግቶት፣
ነገ አልፎልኝ ይላል ማለፉን ረስቶት፣
አይቀር መንፈራገጥ ያሆድ እስኪሞላ፣
ወድቃ እስክትሰበር ህይወት እንደሸክላ
ጣራና ግድግዳው በወርቅ ቢሰራ፣
ገንዘብ ተቆልሎ ቢመስል ተራራ፣
በከፋው ጨለማ በዚያ በሞት መንገድ፣
ተከትሎ አይሄድም ሃብት ስጋ ዘመድ፣
ያለው ከሌለው ጋር ተካፍሎ እንደመብላት፣
ለምን ይሰስታል እድሜ አይለውጥም ሃብት፣
የሌለው ዘመዱን ሸኝቶት በጥርሱ ፣
ችጋር ይዞት ሲሞትው ማልቀሱ።"
ነፍስ ይማር
@Bookfor
@Bookfor
>>Click here to continue<<