ማያልፍ የመሰለኝ ዳምኖ ህይዎቴ
ባዘነብኩት እንባ ታጥቦ ማንነቴ
ግርዶሹ በርትቶ ነገየን ጋርዶብኝ
ፍፁም አንዳልጓጓ ህመም በርትቶብኝ
ዛሬ ነገ እያልኩኝ ሞቴን ሲጠባበቅ
ህመሜን ሳዳምጥ ስሜቶቼን ሳረቅ
.
.
.
መኖር ማለት ስቃይ
መኖር ምለት ህመም
መኖር ማለት ጭንቀት
መኖር ማለት ድካም....
ወደ ተስፋ መንደር እልፍ ጊዜ ባመራ
የ እድሌን ልሻማ ከ እኩዮቼ ጋራ
ብፈልግ... ብጠብቅ ድርሻ የለኝ ሁኖ
ጠብታ እንኳን ሳይቀር ከ እኔነቴ ተኖ
ፀሐይ የለኝ ሁና ሕይዎቴ ዳምኖ
.
.
.
ትላንት በመኖሬ ተስፋ እንኳን ሳይኖረኝ
ምንም ያህል ባዝን የሚያልፍ ባይመስለኝ
ቀን እየቆጠረ ቀን እየጨመረ
የደመናው ጥቁረት መጠኑ ቀንሶ
የስቃይ ዉርጅብኝ ከነበረው አንሶ
ከ ሕይወቴ ጠፋ ቀስ በቀስ ጨርሶ...
.
.
.
የ ፀሐይ ዉበቷ
የፀሐይ ድምቀቷ
የዉበት ፍካቷ
ዛሬ ላይ ብሸፈን
ደመናው ሲገፈፍ ወደጎን ሲበተን....
.
.
.
ህመም ብርድ ሁኖ ያገረጣው ትናንት
ተንፏቆ እየዳሀ ዛሬን በመጠጋት
አንድ ቀን ልጨምር ብዬ በመኖሬ
ተስፋ ፀሐይ ሁኖ ከች አለልኝ ዛሬ!!
📆ሚያዚያ 25 - 2016
✍ዘይድ ሁሴን
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
>>Click here to continue<<