❖ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ❖
"አዳምን የፈጠሩ እጆች በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ ፡ ወዮ ፤ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ ፡ ወዮ ፤ በአዳም ፊት የህይወት መንፈስን እፍ ያለ አፍ ከሃሞት ጋራ የተቀላቀለ የኮመጠጠ መፃፃን ጠጣ ፡ ወዮ ፤ የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው? ምን ከንፈር ነው? ምን አንደበት ነው? የፍቅር ጌታ ሕማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል ፡ ህሊናም ይመታል ፡ ነፍስም ትንቀጠቀጣለች ፡ ስጋም ይደክማል፡፡ የማይሞተው ሞተ ፡ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ ፡ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ ፤ የምትወዱት ሰወች ፈፅሞ አልቅሱለት ፤ ወየው ወየው ወየው አማኑኤል አምላካችን፡፡ ወየው ወየው ወየው መድሃኒታችን ኢየሱስ ፤ ወየው ወየው ወየው ንጉሳችን ክርስቶስ ፤ ወየው ወየው ወየው ፃድቃን ከእንጨት አወረዱት ስጋውንም ለመገነዝ ከርቤ የሚባል የጣፈጠ ሽቱንና ንፁህ በፍታን አመጡ፡፡ ሞተም ተቀበረም ፤ ሙስና ሳይኖርበት ከሙታን ተለይቶ ፈፅሞ ተነሳ ፤ ከሃጢአት ቀንበርም ነፃ አደረገን ፤ በዚያች ስጋ በመለኮት ሃይል ወደ ሰማይ ወደ ቀደመ አኗኗሩ አረገ፡፡"
>>Click here to continue<<