አምቦ ዩኒቨርሲቲ የአዲስ ገቢ ተማሪዎች ምዝገባ በጊዚያዊነት ሰኔ 24 እና 25/2013 ዓ.ም መሆኑን ገልጿል።
ከሰኔ 06 እስከ ሰኔ 20/2013 ዓ.ም ልዩ የምርጫ እረፍት ጊዜ መሆኑንም ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
ይሁን እንጂ ወደየመጡበት አካባቢ መሄድ የማይፈልጉ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው መቆየት እንደሚችሉ እና የተማሪዎች አገልገሎትም እንደማይቋረጥ የዩኒቨርሲቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ መንግስቱ ቱሉ ባላቻ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።
ከምርጫው በኋላ የነባር መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ ሰኔ 21 እና 22/2013 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
@tikvahuniversity @TikvahUniversityybot
>>Click here to continue<<