"...የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዴት በምርጫው ይሳተፉ በሚለው መንገድ ላይ የተወሰነ ነገር የለም" - የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለ @tikvahuniversity
ከቅድመ ምረቃ ጀምሮ በዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ተማሪዎች እንዴት በምርጫው የሚሳተፉበት መንገድ ላይ በሚለው ጉዳይ ላይ የተወሰነ ነገር አለመኖሩን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ለ @tikvahuniversity ገልጿል።
በጉዳዩ ላይ ውሳኔውን በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ/መግለጫም እንደሚሰጥ ነው የገለፀልን።
በሌላ በኩል የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ የተመደቡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ቅሬታ ማቅረቢያ ግዜ ዛሬ ማብቃቱን አሳውቋል።
ቅሬታዎችን ዛሬም ሲቀበል መዋሉን የገለፀው ሚኒስቴሩ ፤ ከዛሬ በኋላ ምንም አይነት ቅሬታ እንደማይቀበል ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል።
አዲስ የተመደቡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ያላቸውን ቅሬታ በድረ ገጽ፣ በኢ-ሜይል እና በስልክ ላለፋት አምስት ቀናት ለሚኒስቴሩ ሲያቀርቡ ቆይተዋል።
@tikvahuniversity @tikvahethiopia
>>Click here to continue<<