TG Telegram Group & Channel
Abel Birhanu የወይኗ ልጅ | United States America (US)
Create: Update:

የዩናይትድ ስቴትስ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ በእስያ ጉዟቸው ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ዩናይትድ ስቴትስ “ዋጋ ትከፍላለች” ስትል ቻይና ዛሬ አስጠንቅቃለች። ፔሎሲ በይፋ ወደ ታይዋን መጓዛቸውን ባያረጋግጡም የዩናይትድ ስቴትስ እና ታይዋን መገናኛ ብዙኃን ይህንን እየዘገቡ ይገኛሉ። የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሀው ቹንይንግ ቤጂንግ ላይ ዛሬ በሰጡት መደበኛ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት “የቻይናን ሉዓላዊ የፀጥታ ጥቅሞች ለማዳከም አሜሪካ ለምትወስደው ርምጃ ኃላፊነቱን ትወስዳለች» ብለዋል። ፔሎሲ በርግጥ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ከ 25 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎነኙ ከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣን ይሆናሉ። ቻይና ታይዋንን የራሷ አንድ አካል አድርጋ የምታይ ሲሆን ታይዋን ግን ራሷን እንደ ነፃ እና ዲሞክራሲያዊት ሀገር አድርጋ ታያለች። የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝትን በተመለከተ ዩናይትድ ስቴትስ ቤጂንግን ለማስቆጣት ሆን ብላ ያደረገችው ነው ስትል ሩሲያ ዛሬ ለቻይና ድጋፏን አሳይታለች። ፔሎሲ ዛሬ ማሌዢያ ኩዋላ ላምፑርን ጎብኝተው ከማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢስማኢል ሳብሪ ጋር እንደተገናኙ የፈረንሳይ ዜና ምንጭ ዘግቧል። የታይዋን የዜና ምንጮች እንደዘገቡት ናንሲ ፔሎሲ ዛሬ ማምሻውን ታይዋን ይገባሉ።

# DW Amharic

የዩናይትድ ስቴትስ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ናንሲ ፔሎሲ በእስያ ጉዟቸው ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ዩናይትድ ስቴትስ “ዋጋ ትከፍላለች” ስትል ቻይና ዛሬ አስጠንቅቃለች። ፔሎሲ በይፋ ወደ ታይዋን መጓዛቸውን ባያረጋግጡም የዩናይትድ ስቴትስ እና ታይዋን መገናኛ ብዙኃን ይህንን እየዘገቡ ይገኛሉ። የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሀው ቹንይንግ ቤጂንግ ላይ ዛሬ በሰጡት መደበኛ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት “የቻይናን ሉዓላዊ የፀጥታ ጥቅሞች ለማዳከም አሜሪካ ለምትወስደው ርምጃ ኃላፊነቱን ትወስዳለች» ብለዋል። ፔሎሲ በርግጥ ታይዋንን የሚጎበኙ ከሆነ ከ 25 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎነኙ ከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣን ይሆናሉ። ቻይና ታይዋንን የራሷ አንድ አካል አድርጋ የምታይ ሲሆን ታይዋን ግን ራሷን እንደ ነፃ እና ዲሞክራሲያዊት ሀገር አድርጋ ታያለች። የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝትን በተመለከተ ዩናይትድ ስቴትስ ቤጂንግን ለማስቆጣት ሆን ብላ ያደረገችው ነው ስትል ሩሲያ ዛሬ ለቻይና ድጋፏን አሳይታለች። ፔሎሲ ዛሬ ማሌዢያ ኩዋላ ላምፑርን ጎብኝተው ከማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢስማኢል ሳብሪ ጋር እንደተገናኙ የፈረንሳይ ዜና ምንጭ ዘግቧል። የታይዋን የዜና ምንጮች እንደዘገቡት ናንሲ ፔሎሲ ዛሬ ማምሻውን ታይዋን ይገባሉ።

# DW Amharic


>>Click here to continue<<

Abel Birhanu የወይኗ ልጅ




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)