TG Telegram Group & Channel
Abdu & Hasu | United States America (US)
Create: Update:

#የአላህ_ፍራቻ

ሰውነቱ በጣም ልዩ የሆነ ሚስክ ሽቶ ጠረን የሚወጣው ሰው ነበር። አንድ ወዳጁ አንድ ቀን እንዲህ ሲል ጠየቀው፡- “ሁልጊዜ በአንተ ላይ የሚሸተው ይህ አስደናቂ መዓዛ ምንድን ነው? ደጋግመህ ስትጠቀም ለሚስክ ሽቶ ብዙ ገንዘብ እያወጣህ መሆን አለበት?” ሰውየውም “በአላህ እምላለሁ! ሚስክን ገዝቼ አላውቅም አረ ተቀብቼውም አላውቅ!” ጓደኛውም በመገረም “ታዲያ መዓዛህ ከየት የመጣ ነው?” ሲል ጠየቀው። ጥያቄውን ለመመለስ ፍላጎት ስላልነበረው “ለምን ትጠይቀኛለህ?” አለው። ጓደኛው “በምትነግረኝ ነገር አላህ ተዓላ በሆነ መንገድ እንድጠቀም እንደሚፈቅድልኝ ተስፋ አደርጋለሁ” ሲል ገለጸ። በጓደኛው ንግግር በመገፋፋት፤ በመጨረሻም የሚከተለውን ነገረው። "በወጣትነቴ በጣም ቆንጆ ልጅ ነበርኩ። አባቴ ነጋዴ ነበር እና ጊዜዬን እሱን በማገዝ አሳልፋለሁ። አንድ ቀን አንዲት አሮጊት ሴት ወደ ሱቅ መጥታ ጨርቅ ገዛች፤ ገንዘቡን የምትከፍልበት ገንዘብ ስላልያዘች አባቴን አብሮ ቤቷ ሄዷ ብር የሚቀበል ሰው እንዲያዘጋጅ ነገረችው። አባቴ አብሪያት እንድሄድ ነገረኝና አንድ ትልቅ ቤተ መንግሥት ፊት እስክንቆም ድረስ ተከተልኳት። አሮጊቷ ወደ ሚገርም ግቢ አስገቡኝ፤ ስገባ እይታዬ ወደ አንዲት ቆንጆ ወጣት ልጅ ሆነ ከሐር ትራስ ላይ ከፍ ባለ ወንበር ላይ ተቀምጣለች። ባየችኝ ቅጽበት፣ በውበቴ ደነገጠች እና አብሪያት እንድቀመጥ ጠየቀች። እኔም እምቢ አልኩኝ፤ የእኔ እምቢተኝነት ወደ እኔ እንድትወርድ አነሳሳት። ከዚያም በፍቅር ስሜት እየጎተተች ወደ ራሷ እንድቀርብ ታረገኝ ጀመር። በእውነተኛ ችግር ውስጥ ነበርኩ። ከእቅፏ ለማምለጥ መጸዳጃ ቤት መጠቀም እችል እንደሆነ ጠየቅኋት። ትዕግሥት ብታጣም ወደ መጸዳጃ ቤት መራችኝ፤ መጸዳጃ ቤት ከገባሁ ቡሀላ በሰውነቴ፣ በልብሴ እና በፊቴ ላይ ቆሻሻ ቀባሁ። ከመጸዳጃ ቤት ስወጣ በጉጉት የምትጠብቀው ልጅ የመልከ መልካም ወጣት ሳይሆን በሰው ቆሻሻ የተሸፈነ ሰው እይታ እና ሽታ ተቀበለች! የፍላጎቷ ነበልባል፣ በአንድ ጊዜ፣ ጠፋ እና ለአገልጋዮቿ በፍርሃት እና በመጸየፍ ጮኸች፣ “ይህ እብድ ነው! ወደ ውጪ ጣሉት!” አለች፤ ያለምንም ችግር ወደ ውጪ ወጣሁ በአጋጣሚ ከእኔ ጋር አንድ ዲርሃም ነበረኝ። ስሄድ ሳሙና ገዛሁ እና ወደ ወንዙ ወርጄ ሰውነቴን እና ልብሴን ከቆሻሻ ከአጸዳሁ ቡሀላ ወደ አባቴ ተመለስኩ ግን ስለተፈጠረው ነገር አንድም ቃል አልተናገርኩም። በዚያ ሌሊት አንድ ጥሩ መዓዛ ያለው መልከ መልካም ሰው ወደ እኔ የመጣበትን ሕልም አየሁ። ማን እንደሆነ ጠየቅኩት እሱም ጅብሪል (ዐለይሂ ሰላም) ነው ሲል መለሰልኝ። እንዲህም አለኝ፡- “አላህ ተአላ ጀናን እንዳበስርህና ሽቶዋን እንዳረግብህ ላከኝ በኃጢአት ላለመውድቅ ባደረግከው ድርጊት አላህ ተደስቷል። ከዚያም እጆቹ በፊቴ፣ ሰውነቴና ልብሴ ላይ አልፎ ሄደ። በማግስቱ ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ፣ እስከ ዛሬ ድረስ ከሰውነቴ ውስጥ ለዘላለም የሚሸተውን ጥሩ መዓዛ አገኘሁ።"

(አት-ተርጊብ ወተረሂብ ሊል ያፊኢ ገጽ-165)

@abduftsemier
@abduftsemier

#የአላህ_ፍራቻ

ሰውነቱ በጣም ልዩ የሆነ ሚስክ ሽቶ ጠረን የሚወጣው ሰው ነበር። አንድ ወዳጁ አንድ ቀን እንዲህ ሲል ጠየቀው፡- “ሁልጊዜ በአንተ ላይ የሚሸተው ይህ አስደናቂ መዓዛ ምንድን ነው? ደጋግመህ ስትጠቀም ለሚስክ ሽቶ ብዙ ገንዘብ እያወጣህ መሆን አለበት?” ሰውየውም “በአላህ እምላለሁ! ሚስክን ገዝቼ አላውቅም አረ ተቀብቼውም አላውቅ!” ጓደኛውም በመገረም “ታዲያ መዓዛህ ከየት የመጣ ነው?” ሲል ጠየቀው። ጥያቄውን ለመመለስ ፍላጎት ስላልነበረው “ለምን ትጠይቀኛለህ?” አለው። ጓደኛው “በምትነግረኝ ነገር አላህ ተዓላ በሆነ መንገድ እንድጠቀም እንደሚፈቅድልኝ ተስፋ አደርጋለሁ” ሲል ገለጸ። በጓደኛው ንግግር በመገፋፋት፤ በመጨረሻም የሚከተለውን ነገረው። "በወጣትነቴ በጣም ቆንጆ ልጅ ነበርኩ። አባቴ ነጋዴ ነበር እና ጊዜዬን እሱን በማገዝ አሳልፋለሁ። አንድ ቀን አንዲት አሮጊት ሴት ወደ ሱቅ መጥታ ጨርቅ ገዛች፤ ገንዘቡን የምትከፍልበት ገንዘብ ስላልያዘች አባቴን አብሮ ቤቷ ሄዷ ብር የሚቀበል ሰው እንዲያዘጋጅ ነገረችው። አባቴ አብሪያት እንድሄድ ነገረኝና አንድ ትልቅ ቤተ መንግሥት ፊት እስክንቆም ድረስ ተከተልኳት። አሮጊቷ ወደ ሚገርም ግቢ አስገቡኝ፤ ስገባ እይታዬ ወደ አንዲት ቆንጆ ወጣት ልጅ ሆነ ከሐር ትራስ ላይ ከፍ ባለ ወንበር ላይ ተቀምጣለች። ባየችኝ ቅጽበት፣ በውበቴ ደነገጠች እና አብሪያት እንድቀመጥ ጠየቀች። እኔም እምቢ አልኩኝ፤ የእኔ እምቢተኝነት ወደ እኔ እንድትወርድ አነሳሳት። ከዚያም በፍቅር ስሜት እየጎተተች ወደ ራሷ እንድቀርብ ታረገኝ ጀመር። በእውነተኛ ችግር ውስጥ ነበርኩ። ከእቅፏ ለማምለጥ መጸዳጃ ቤት መጠቀም እችል እንደሆነ ጠየቅኋት። ትዕግሥት ብታጣም ወደ መጸዳጃ ቤት መራችኝ፤ መጸዳጃ ቤት ከገባሁ ቡሀላ በሰውነቴ፣ በልብሴ እና በፊቴ ላይ ቆሻሻ ቀባሁ። ከመጸዳጃ ቤት ስወጣ በጉጉት የምትጠብቀው ልጅ የመልከ መልካም ወጣት ሳይሆን በሰው ቆሻሻ የተሸፈነ ሰው እይታ እና ሽታ ተቀበለች! የፍላጎቷ ነበልባል፣ በአንድ ጊዜ፣ ጠፋ እና ለአገልጋዮቿ በፍርሃት እና በመጸየፍ ጮኸች፣ “ይህ እብድ ነው! ወደ ውጪ ጣሉት!” አለች፤ ያለምንም ችግር ወደ ውጪ ወጣሁ በአጋጣሚ ከእኔ ጋር አንድ ዲርሃም ነበረኝ። ስሄድ ሳሙና ገዛሁ እና ወደ ወንዙ ወርጄ ሰውነቴን እና ልብሴን ከቆሻሻ ከአጸዳሁ ቡሀላ ወደ አባቴ ተመለስኩ ግን ስለተፈጠረው ነገር አንድም ቃል አልተናገርኩም። በዚያ ሌሊት አንድ ጥሩ መዓዛ ያለው መልከ መልካም ሰው ወደ እኔ የመጣበትን ሕልም አየሁ። ማን እንደሆነ ጠየቅኩት እሱም ጅብሪል (ዐለይሂ ሰላም) ነው ሲል መለሰልኝ። እንዲህም አለኝ፡- “አላህ ተአላ ጀናን እንዳበስርህና ሽቶዋን እንዳረግብህ ላከኝ በኃጢአት ላለመውድቅ ባደረግከው ድርጊት አላህ ተደስቷል። ከዚያም እጆቹ በፊቴ፣ ሰውነቴና ልብሴ ላይ አልፎ ሄደ። በማግስቱ ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ፣ እስከ ዛሬ ድረስ ከሰውነቴ ውስጥ ለዘላለም የሚሸተውን ጥሩ መዓዛ አገኘሁ።"

(አት-ተርጊብ ወተረሂብ ሊል ያፊኢ ገጽ-165)

@abduftsemier
@abduftsemier


>>Click here to continue<<

Abdu & Hasu




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)