TG Telegram Group & Channel
Abdu & Hasu | United States America (US)
Create: Update:

#ከሰይዲ_ማዕድ

ሰይድ ሚቅባስ ወጣት ሳሉ የመንግስት ሥራ ጀምረው ነበር። ሥራው ግን የአዕምሮ እረፍት አልሰጣቸውም። ይሄ ሥራ ከነቢ መንገድ ጋር አብሮ ባይሄድስ ብለው ይሰጉ ነበር። አንድ ቀን ስጋታቸው ባስ አለና ጉድ እንዳልሆን በሚል ጭንቀት ሲያለቅሱ ዋሉ። የዛን እለት ማታ ታድያ እንቅልፍ ሸለብ እንዳደረጋቸው በህልማቸው እንዲህ ሆነ። አንድ ሰውዬ ይመጣና "ረሱል ይፈልጉሃል!" ይላቸዋል። በፍጥነት ብድግ ብለው "መርሐባ መርሐባ የት ናቸው?" ሲሉ ወደ አንድ ክፍል አመላከታቸው። እየተጣደፉ ሲገቡ ክፍሉ ባዶ ነበር። ሌላ ክፍል ከፍተው ሲገቡ አንድ ሰው ወንበር ላይ ተቀምጦ አዩ። ያ ሰው ሰይድ አቡበክር ሲዲቅ ረ.ዓ ናቸው። ወለላው ነቢ ደግሞ በተፈጠሩበት፣ በተወለዱበት መልክ አልጋ ላይ አረፍ ብለዋል። ውዱን ሰው በተኸለቁበት መልክ ማየታቸው ሆዳቸውን ቢያማታው እያለቀሱ በእንብርክክ፣ በዳዴ፣ በእንፉቅቅ ወደ አልጋው ይንደረደሩ ጀመር። ሊደርሱ ትንሽ ሲቀራቸው የኔ ነቢ አፈፍ አደረጓቸውና "ያንተ ጀነት’ኮ ከእኔና ከአቡበክር ጋር ነው!" አሏቸው። ሲነቁ ህልም ነው። ሲነጋ ለባለቤታቸው ወስያ መስጠት እንደሚፈልጉ ይነግሯቸዋል። ምክንያቱን ሲጠይቋቸውም "በቃ እኔ ልሞት ነው!" ብለው ከህልሙ የተረዱ የመሰላቸውን ፍቺ ይነግሯቸዋል። ያንን ቀን ከነቢና ከአቡበክር ጎን እንደሚሆኑ ከዛ ማር አንደበት የሰሙትን ብስራት እያሰቡ ሲስቁ፣ ወዲህ ደግሞ ከአባታቸው መለየትን እያስታወሱ ሲያለቅሱ ዋሉ። በሁኔታቸው የተደናገጡትና የእሜቴ አዒሻ ሞክሼ የሆኑት ባለቤታቸው ዱዓ ብለው በግ አስመጡ። ሁነኛ ሰውም አስጠሩ። ሰይድ ሙሒቡ መጡና ምን እንደተፈጠረ ጠየቋቸው። ይሄኔ እናት አዒሻ ሰይዲ ህልም ማየታቸውንና እሞታለሁ ብለው ማሰባቸውን ነግረው ዱዓ እንዲያደርጉላቸው ጠየቋቸው። ሰይድ ሙሒቡ "ህልሙን ልስማው" ብለው አጥብቀው ያዟቸው። ሰይድ ሙሒቡ ህልሙን ሲሰሙ ሳቁ። "ታድያ የዚህ መናም ፍቺ’ኮ እርስዎ እንዳሰቡት የሞት አይደለም። የመንግስት ሥራ ቀጥተኛውን መንገድ ያስተኛል ብለው ሲሰጉ ስለነበር ቀንዎ ሲደርስ ኺታምዎ የሚሆነው ከነርሱ ጋር መሆኑን ነግረው አይስጉ እያሉዎ፣ እያባሸሩዎ ነው።" አሏቸው። ደስታ ሆነ። ለዱዓ የታሰበው በግ ለሹኩር ታረደ። ለካ የዋሻውን እግረኛ ሲዲቁል አክበርን "አትዘን አላህ ከ’ኛ ጋር ነው" እንዳሏቸው አብሽር አንተ ከ’ኛ ጋር ነህ ብለው ቀድመው እያባሸሯቸው ኖሯል። ለነገሩ ጌትዬውስ በወለላው ቃሉ "ላኸውፉን ዓለይሂም ወላሁም የህዘኑን!" ያለው እነሱን አይደል? በሁለቱም ዓለም ፍርሃት የለባቸው፣ ጭንቅ አያገኛቸው!
ሰይደቲ_አቲቃ

አሏሁመ ሶሊ አላ ሰይዲና ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ ወሰለም💚💚💚
@abduftsemier
@abduftsemier

#ከሰይዲ_ማዕድ

ሰይድ ሚቅባስ ወጣት ሳሉ የመንግስት ሥራ ጀምረው ነበር። ሥራው ግን የአዕምሮ እረፍት አልሰጣቸውም። ይሄ ሥራ ከነቢ መንገድ ጋር አብሮ ባይሄድስ ብለው ይሰጉ ነበር። አንድ ቀን ስጋታቸው ባስ አለና ጉድ እንዳልሆን በሚል ጭንቀት ሲያለቅሱ ዋሉ። የዛን እለት ማታ ታድያ እንቅልፍ ሸለብ እንዳደረጋቸው በህልማቸው እንዲህ ሆነ። አንድ ሰውዬ ይመጣና "ረሱል ይፈልጉሃል!" ይላቸዋል። በፍጥነት ብድግ ብለው "መርሐባ መርሐባ የት ናቸው?" ሲሉ ወደ አንድ ክፍል አመላከታቸው። እየተጣደፉ ሲገቡ ክፍሉ ባዶ ነበር። ሌላ ክፍል ከፍተው ሲገቡ አንድ ሰው ወንበር ላይ ተቀምጦ አዩ። ያ ሰው ሰይድ አቡበክር ሲዲቅ ረ.ዓ ናቸው። ወለላው ነቢ ደግሞ በተፈጠሩበት፣ በተወለዱበት መልክ አልጋ ላይ አረፍ ብለዋል። ውዱን ሰው በተኸለቁበት መልክ ማየታቸው ሆዳቸውን ቢያማታው እያለቀሱ በእንብርክክ፣ በዳዴ፣ በእንፉቅቅ ወደ አልጋው ይንደረደሩ ጀመር። ሊደርሱ ትንሽ ሲቀራቸው የኔ ነቢ አፈፍ አደረጓቸውና "ያንተ ጀነት’ኮ ከእኔና ከአቡበክር ጋር ነው!" አሏቸው። ሲነቁ ህልም ነው። ሲነጋ ለባለቤታቸው ወስያ መስጠት እንደሚፈልጉ ይነግሯቸዋል። ምክንያቱን ሲጠይቋቸውም "በቃ እኔ ልሞት ነው!" ብለው ከህልሙ የተረዱ የመሰላቸውን ፍቺ ይነግሯቸዋል። ያንን ቀን ከነቢና ከአቡበክር ጎን እንደሚሆኑ ከዛ ማር አንደበት የሰሙትን ብስራት እያሰቡ ሲስቁ፣ ወዲህ ደግሞ ከአባታቸው መለየትን እያስታወሱ ሲያለቅሱ ዋሉ። በሁኔታቸው የተደናገጡትና የእሜቴ አዒሻ ሞክሼ የሆኑት ባለቤታቸው ዱዓ ብለው በግ አስመጡ። ሁነኛ ሰውም አስጠሩ። ሰይድ ሙሒቡ መጡና ምን እንደተፈጠረ ጠየቋቸው። ይሄኔ እናት አዒሻ ሰይዲ ህልም ማየታቸውንና እሞታለሁ ብለው ማሰባቸውን ነግረው ዱዓ እንዲያደርጉላቸው ጠየቋቸው። ሰይድ ሙሒቡ "ህልሙን ልስማው" ብለው አጥብቀው ያዟቸው። ሰይድ ሙሒቡ ህልሙን ሲሰሙ ሳቁ። "ታድያ የዚህ መናም ፍቺ’ኮ እርስዎ እንዳሰቡት የሞት አይደለም። የመንግስት ሥራ ቀጥተኛውን መንገድ ያስተኛል ብለው ሲሰጉ ስለነበር ቀንዎ ሲደርስ ኺታምዎ የሚሆነው ከነርሱ ጋር መሆኑን ነግረው አይስጉ እያሉዎ፣ እያባሸሩዎ ነው።" አሏቸው። ደስታ ሆነ። ለዱዓ የታሰበው በግ ለሹኩር ታረደ። ለካ የዋሻውን እግረኛ ሲዲቁል አክበርን "አትዘን አላህ ከ’ኛ ጋር ነው" እንዳሏቸው አብሽር አንተ ከ’ኛ ጋር ነህ ብለው ቀድመው እያባሸሯቸው ኖሯል። ለነገሩ ጌትዬውስ በወለላው ቃሉ "ላኸውፉን ዓለይሂም ወላሁም የህዘኑን!" ያለው እነሱን አይደል? በሁለቱም ዓለም ፍርሃት የለባቸው፣ ጭንቅ አያገኛቸው!
ሰይደቲ_አቲቃ

አሏሁመ ሶሊ አላ ሰይዲና ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ ወሰለም💚💚💚
@abduftsemier
@abduftsemier


>>Click here to continue<<

Abdu & Hasu




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)