TG Telegram Group & Channel
ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy | United States America (US)
Create: Update:

ብቸኝነትን የመረጥኩት....
ካህሊል ጂብራን

"ከአለም ተነጥለህ ብቻህን ለመኖር እንዴት መረጥክ ?"
ብዬ ጠየኩት

በሀሳብ ተውጦ በዝምታ ከቆየ በኋላ እንዲህ አለ

‹‹በፍጥረቶቹ መካከል እየኖርኩ እግዚአብሔርን ማምለክ እችል ነበር፤ ማምለክ ለብቻ ተነጥሎ መኖርን አይጠይቅምና! ሰዎችን የተውኳቸው እግዚአብሔርን ለማግኘት ስል አልነበረም፡፡ በአባትና በእናቴ ቤት ሆኜም አገኘው ነበር፡፡ ከሰዎች የተገለልኩበት ምክንያት ተፈጥሯቸው ከእኔ ተፈጥሮአዊ ባህርይ ጋር ስለተጋጨ እንዲሁም ህልማቸው ከህልሜ ጋር ባለመስማማቱ ነው፡፡

‹‹ብቸኝነትን የፈለግሁት ራሳቸውን ሽጠው በተመሳሳይ ዋጋ በመንፈሳዊም ሆነ በቁስ አካላዊ መስፈርት ከእነሱ ያነሰች ነገርን የሚገዙ ሰዎችን ፊት ላለማየት ስል ነው...

‹‹ብቸኝነትን የፈለግሁት የዕውቀትን መንፈስ በህልሞቻቸው ውስጥ አይተው ግባቸውን እንደመቱ ከሚያምኑት ከእነዚያ በራሳቸው ከሚረኩት ሰዎች እራሴን ለመሸሸግ ስል ነው...

‹‹ከማህበረሰቡ የሸሸሁት እውነትን ባያዩም መንፈሱን ባይገነዘቡትም እና ለዓላማቸው መሳካት ሲሉ ብቻ የእውነትን ፍሬ ነገር ሙሉ ለሙሉ እንዳገኙት አድርገው ከሚለፍፉት ለመራቅ ነው::

‹‹ከዓለም ተነጥዬ ብቸኝነትን የፈለግሁበት ምክንያት ትህትናን ደካማነት፣ ምህረትን ፍርሃት፣ ትምክህትን ደግሞ የጥንካሬ መገለጫ እንደሆነ አድርገው የሚያምኑትን ህዝቦች በይሉኝታ መቅረቡ አሰልችቶኝ ነው፡፡

‹ብቸኝነትን የመረጥኩት ነፍሴ ከነዚያ ፀሐይ፣ ጨረቃ እንዲሁም ከዋክብት በገንዘብ ካዝናዎቻቸው ውስጥ ቢሆኑ ኖሮ እንደማይወጡና በእነሱ የአትክልት ስፍራዎች ውስጥ ካልሆነ በስተቀር እንደማይጠልቁ ፅኑ እምነት ካላቸው ጋር አብሮ መኖሩ ስላንገፈገፈኝ ነው...

‹‹እናም በዓይኖቻቸው ላይ ወርቃማ አቧራ እየጨመሩና ጆሮቻቸውን ትርጉም አልባ በሆኑ ወሬዎች እየሞሉ የህዝቦችንን ምድራዊ ዕጣ ፈንታ ከሚበጠብጡት የስልጣን ጥመኞች ሸሸሁ

‹‹እንደስብከታቸው የማይኖሩትን እና ህዝቦችን እነሱ የማይፈጽሙትን ነገር እንዲያደርጉ የሚመክሩትን (የሚያስገድዱትን) ቀሳውስት ለመሽሽ ስል ትቻቸው ሄድኩ...

‹‹ሰዎች ስልጣኔ ብለው የሚጠሩትን  ትቼ እዚህ የምኖረው ስሮቹ መሬት ስር ተሸሽገው የተቆላለፉ ቅርንጫፎቹ ከደመናው በላይ ከፍ ብለው ፈክተው፣ የበቀሉት አበቦቹ ግን ስስት፣ ክፋት እና ሰቃይ የሆኑ ብልሹ የሆነ ጠንካራ አስቀያሚ ዛፍ ሆኖ ስላገኘሁት ነው፡፡

‹‹ብቸኝነትን የፈለግሁት እዚህ በውስጡ ለመንፈስ፣ ለልብና ለአካል የሚሆን ሙሉ ህይወት ስላለ ነው:: እናም የፀሐይ ብርሃን የሚያርፍባቸውና መጨረሻ የሌላቸው አበቦች መዓዛቸውን ወደ ህዋ የሚተነፍሱበት እንዲሁም ጅረቶች እያዜሙ ወደ ባህር የሚያቀኑበትን የሳር መስክ አግኝቻለሁ፡፡ የፀደይ ወራትን ትኩስ ግንዛቤ፣ የክረምትን ቀለመደማቅ ናፍቆት፣ የመኸርን ጣፋጭ መዝሙሮች እና የበጋ ወራትን ውብ እንቆቅልሽ ያገኘሁባቸውን ተራሮች ደረስኩባቸው፡፡ ወደዚህ ርቆ ወደሚገኝ ግዛት የመጣሁት የዓለምን ሚስጥሮች ለማወቅ ስለተራብኩ ነው፡፡

Book: Between night and morn
Author :Khalil Jibran

@zephilosophy

ብቸኝነትን የመረጥኩት....
ካህሊል ጂብራን

"ከአለም ተነጥለህ ብቻህን ለመኖር እንዴት መረጥክ ?"
ብዬ ጠየኩት

በሀሳብ ተውጦ በዝምታ ከቆየ በኋላ እንዲህ አለ

‹‹በፍጥረቶቹ መካከል እየኖርኩ እግዚአብሔርን ማምለክ እችል ነበር፤ ማምለክ ለብቻ ተነጥሎ መኖርን አይጠይቅምና! ሰዎችን የተውኳቸው እግዚአብሔርን ለማግኘት ስል አልነበረም፡፡ በአባትና በእናቴ ቤት ሆኜም አገኘው ነበር፡፡ ከሰዎች የተገለልኩበት ምክንያት ተፈጥሯቸው ከእኔ ተፈጥሮአዊ ባህርይ ጋር ስለተጋጨ እንዲሁም ህልማቸው ከህልሜ ጋር ባለመስማማቱ ነው፡፡

‹‹ብቸኝነትን የፈለግሁት ራሳቸውን ሽጠው በተመሳሳይ ዋጋ በመንፈሳዊም ሆነ በቁስ አካላዊ መስፈርት ከእነሱ ያነሰች ነገርን የሚገዙ ሰዎችን ፊት ላለማየት ስል ነው...

‹‹ብቸኝነትን የፈለግሁት የዕውቀትን መንፈስ በህልሞቻቸው ውስጥ አይተው ግባቸውን እንደመቱ ከሚያምኑት ከእነዚያ በራሳቸው ከሚረኩት ሰዎች እራሴን ለመሸሸግ ስል ነው...

‹‹ከማህበረሰቡ የሸሸሁት እውነትን ባያዩም መንፈሱን ባይገነዘቡትም እና ለዓላማቸው መሳካት ሲሉ ብቻ የእውነትን ፍሬ ነገር ሙሉ ለሙሉ እንዳገኙት አድርገው ከሚለፍፉት ለመራቅ ነው::

‹‹ከዓለም ተነጥዬ ብቸኝነትን የፈለግሁበት ምክንያት ትህትናን ደካማነት፣ ምህረትን ፍርሃት፣ ትምክህትን ደግሞ የጥንካሬ መገለጫ እንደሆነ አድርገው የሚያምኑትን ህዝቦች በይሉኝታ መቅረቡ አሰልችቶኝ ነው፡፡

‹ብቸኝነትን የመረጥኩት ነፍሴ ከነዚያ ፀሐይ፣ ጨረቃ እንዲሁም ከዋክብት በገንዘብ ካዝናዎቻቸው ውስጥ ቢሆኑ ኖሮ እንደማይወጡና በእነሱ የአትክልት ስፍራዎች ውስጥ ካልሆነ በስተቀር እንደማይጠልቁ ፅኑ እምነት ካላቸው ጋር አብሮ መኖሩ ስላንገፈገፈኝ ነው...

‹‹እናም በዓይኖቻቸው ላይ ወርቃማ አቧራ እየጨመሩና ጆሮቻቸውን ትርጉም አልባ በሆኑ ወሬዎች እየሞሉ የህዝቦችንን ምድራዊ ዕጣ ፈንታ ከሚበጠብጡት የስልጣን ጥመኞች ሸሸሁ

‹‹እንደስብከታቸው የማይኖሩትን እና ህዝቦችን እነሱ የማይፈጽሙትን ነገር እንዲያደርጉ የሚመክሩትን (የሚያስገድዱትን) ቀሳውስት ለመሽሽ ስል ትቻቸው ሄድኩ...

‹‹ሰዎች ስልጣኔ ብለው የሚጠሩትን  ትቼ እዚህ የምኖረው ስሮቹ መሬት ስር ተሸሽገው የተቆላለፉ ቅርንጫፎቹ ከደመናው በላይ ከፍ ብለው ፈክተው፣ የበቀሉት አበቦቹ ግን ስስት፣ ክፋት እና ሰቃይ የሆኑ ብልሹ የሆነ ጠንካራ አስቀያሚ ዛፍ ሆኖ ስላገኘሁት ነው፡፡

‹‹ብቸኝነትን የፈለግሁት እዚህ በውስጡ ለመንፈስ፣ ለልብና ለአካል የሚሆን ሙሉ ህይወት ስላለ ነው:: እናም የፀሐይ ብርሃን የሚያርፍባቸውና መጨረሻ የሌላቸው አበቦች መዓዛቸውን ወደ ህዋ የሚተነፍሱበት እንዲሁም ጅረቶች እያዜሙ ወደ ባህር የሚያቀኑበትን የሳር መስክ አግኝቻለሁ፡፡ የፀደይ ወራትን ትኩስ ግንዛቤ፣ የክረምትን ቀለመደማቅ ናፍቆት፣ የመኸርን ጣፋጭ መዝሙሮች እና የበጋ ወራትን ውብ እንቆቅልሽ ያገኘሁባቸውን ተራሮች ደረስኩባቸው፡፡ ወደዚህ ርቆ ወደሚገኝ ግዛት የመጣሁት የዓለምን ሚስጥሮች ለማወቅ ስለተራብኩ ነው፡፡

Book: Between night and morn
Author :Khalil Jibran

@zephilosophy
👍7718🔥5👏2


>>Click here to continue<<

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)