TG Telegram Group & Channel
ዘተዋሕዶ - zetewahedo | United States America (US)
Create: Update:

✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ መስከረም 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞✞✞

+*" ቅዱስጐርጐርዮስ ዘአርማንያ "°+

✞✞✞ ይህ ቅዱስ አባት ከሰማዕታት: ከጻድቃን: ከሊቃውንትና ከዻዻሳት ዝርዝር
ውስጥ ይገኛል:: በቤተ ክርስቲያንም ዓበይትተጽፎ
ከሚባሉ አበው አንዱ ነው:: ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሮማዊ ሲሆን ከክርስቲያን
ወላጆቹ የተወለደው በዘመነ ሰማዕታት (በ3ኛው መቶ
ክ/ዘመን) ነው::

+አበው በትውፊት እንደ ነገሩን ከሆነ ቅዱሱ የታላቁዋ ሰማዕት ቅድስት
አርሴማ ትልቅ ወንድም ነው:: በዜና ሰማዕታት
እንደሚገኘው በዚያ የመከራ ዘመን ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሦስት ኃላፊነቶች
ነበሩበት:-

1.ቅድስት አርሴማን ጨምሮ ደናግሉን ማጽናት
2.ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ ማጥናት
3.የሚመጣውን መከራ ለመቀበል ራሱን ማዘጋጀት::

+ቅዱሱ 3ቱንም ኃላፊነቶች በሚገባ በመወጣቱ ከራሱ አልፎ ለሌሎቹ አርአያ
መሆን ቻለ:: ያቺን ንጽሕት አርበኛ ቅድስት
አርሴማንም አጽንቶ የደናግሉ መሪ አደረጋት:: መከራው በጣም ገፍቶ እስከበመልኩዋ
መጣበት ጊዜ ድረስ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ
ሆነው ይጸልዩ: ይጾሙ: ገዳማዊ ሥራንም ይሠሩ ነበር::

+ለዚህም ነው ቅድስት አርሴማና ቅዱስ ጐርጐርዮስ ጻድቃን የምንላቸው::
በኋላ ግን ማሕደረ ሰይጣን ዲዮቅልጢያኖስ
ተማርኮ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ በማለቱ ቅዱስ ጐርጐርዮስበጸሎት ድንግሏን
አርሴማን ጨምሮ ክርስቲያኖችን ይዞ ወደ አርማንያ
ተሰደደ::

+በአርማንያም በአንድ ገዳም ውስጥ ተደብቀው በጾምና ለጥቂት
ጊዜ ቆዩ: ነገር ግን ረሃብ ፈጃቸው:: የሚላስ
የሚቀመስ ነገር በአካባቢው ባለ መኖሩ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወደ ከተማ
ለመውጣት ተገደደ::

+በዚያም በድርጣድስ ቤተ መንግስት ውስጥ ባርነት ተቀጠረ:: በሚያገኛት
ገንዘብም ወገኖቹን ይረዳ ነበር:: መከራው ግንእኔ
አለቀቃቸውም:: ርጉም ዲዮቅልጢያኖስ ቅዱሳኑ ወደ አርማንያ መሔዳቸውን
ስለ ሰማ ይዞ እንዲልክለት ድርጣድስን ላከው::

+ድርጣድስ ግን ቅድስት አርሴማን ባያት ጊዜ ከውበቷ የተነሳ መታገስ
ባለመቻሉ "ካላገባሁሽ" አላት:: ድንግሊቱ ግን "
የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ: አይሆንም" አለችው:: ሊያስፈራራት ሞከረ:: ዐይኗ እያየ ደናግሉን ጨፈጨፋቸው::

+አልሳካልህ ቢለው በአደባባይ በግድ ሊያገባት ቢሞክር እጁን ጠምዝዛ
በሰው ሁሉ ፊት መሬት ላይ ጣለችው:: እጅግ ስላፈረ
አስገረፋት: አሰቃያት: ዐይኗንም አወጣ:: በመጨረሻም አንገቷን አስቆርጦ
ከሰማዕታቱ ጋር ተራራ ላይ ጣላት::

+ወዲያው ደግሞ የቅዱስ ጐርጐርዮስ ማንነቱ በመታወቁ ይዘው
እስኪያልቅ ገረፉት:: በእሳትም አቃጠሉት:: በብዙሽማግሌ
ስቃይም አሰቃዩት::

+በመጨረሻ ግን ከነ ሕይወቱ እንዲቀበር ተወሰነበት:: ወደ መጸዳጃ ቤት
ወስደውም ከነ ሕይወቱ ቀበሩት:: ነገር ግን
የእግዚአብሔር መልአክ ወርዶ መተንፈሻ ቀዳዳን ሠራለት:: አንዲት
ክርስቲያንም በዚያች ቀዳዳ ቂጣ እየጣለችለት ለ15
ዓመታት ተቀብሮ ኖረ::

+አካሉና አፈሩ ተጣበቀ:: እርሱ ግን ፈጣሪውን እያመሰገነ ቆየ:: ከነገርየንጉሡ ሁሉ በኋላ ድርጣድስና
ባለሟሎቹ ለአደን
በሔዱበት ርኩስ መንፈስ ወደ አውሬነት (እሪያነት) ቀየራቸው::

+የንጉሡ እንስሳ /አውሬ መሆን በአርማንያ ታላቅ ድንጋጤን ፈጠረ::
እህት ስታለቅስ በራዕይ "ለእመ ኢያዕረግምዎ
ለጐርጐርዮስ አልብክሙ ድኂን-ጐርጐርዮስን ከተቀበረበት ካላወጣችሁት
አትድኑም" አላቸው:: ወዲያውም በዚያች ሽማግሌ መሪነት
ቆፍረው አወጡት::

+አካሉንም እግዚአብሔር መለሰለት:: ቅዱሱ እንደ ወጣ ዕረፍትን አልፈለገም::
ለ15 ዓመታት ቀባሪ አጥቶ የተበተነውን
የቅድስት አርሴማንና የሰማዕታቱን አጽም ሰብስቦ በክብር አኖረው::
ድርጣድስና ባለሟሎቹንም ወደ በርሃ ሒዶ ፈወሳቸው::

+ወደ ሰውነትም መልሶ መላ አርማንያን ወደ ክርስትና መለሰ:: የንጉሡን እግር ግን የአውሬ አድርጐት ቀርቷል:: በመጨረሻም
ቅዱስ ጐርጐርዮስ የአርማንያ ሊቀ ዻዻሳት ሆኖ ተሹሞ ብዙ መጻሕፍትን
ደረሰ:: ከ318ቱ ሊቃውንትም አንዱ ሆኖ ተቆጠረ::
ዕረፍቱ ታሕሳስ 15 ቀን ሲሆን ዛሬ ከተቀበረበት የወጣበት ነው::

+" ቅዱስ ቂርቆስ ገዳማዊ "+

+ቅዱሱ የ6ኛው መቶ ክ/ዘመን ጻድቅ ሲሆን በዓለም ከመናፍቃን: በገዳም
ደግሞ ከአጋንንት ብዙ መከራን ተቀብሏል:: በወቅቱ
መለካውያን (የአሁኖቹ ካቶሊኮችና ምስራቅ ኦርቶዶክሶች) አባቶችን
ያሳድዱ ነበር:: ልክ 9ኙ ቅዱሳን በዚህ
ምክንያት ወደ ኢትዮዽያ እንደመጡት ቅዱስ ቂርቆስም ወደ ግብጽ በርሃ ከእርሷ ተሰደደ::

+በበርሃው ውሃም ሆነ ዛፍ ባለመኖሩ በረሃብና በጥም በመሰቃየቱ ወደ ፈጣሪ
ለመነ:: ጌታም አንዲት አጋዘን ልኮለት
ወተትን አልቦ ጠጣ:: እስከ ሕይወቱ ፍጻሜም ምግቡ ይሔው የአጋዘን ወተት
ነበር:: በዚህ ምክንያት ይሔው ዛሬም ድረስ "
ቅዱስ ቂርቆስ ገዳማዊ ዘሲሳዩ ሐሊበ ቶራ" እየተባለ ይጠራል::

+በበርሃው ውስጥ በኖረባቸው ዘመናትም አንድም ሰው አይቶ ካለማወቁስትሆን
ባለፈ አጋንንት በገሃድ እየመጡ ያሰቃዩት ነበር::
ቅዱሱ ግን በትእግስት ኑሮ በዚህች ቀን ሲያርፍ ብዙ ተአምራት በበዓቱ
ውስጥ ተገልጠዋል:: ይህንን ያዩት ደግሞ ከዻዻሱ
ዘንድ ተልከው የቀበሩት አበው ናቸው::

+" ቅድስት ሮማነ ወርቅ "+

+ይህቺ ቅድስት እናት ደግሞ ኢትዮዽያዊት ናት:: የነገሥታቱ ልጅ አባቷ
አፄ ናዖድ: እናቷ ደግሞ እሌኒ /ወለተ
ማርያም ይባላሉ:: ወንድሟ ደግሞ አፄ ልብነ ድንግል ይባላሉ::

+በቤተ መንግስት ውስጥ ብታድግም መንፈሳዊነቷ የገዳም ያህል ነበር::
ከተባረከ ትዳሯም ቅዱስ ላዕከ ማርያምን አፍርታለች::
አብያተ ክርስቲያናትን ከማነጽ ባለፈ የነዳያን እናትም ነበረች:: በክርስትናዋ
ፈጣሪዋን ደስ አሰኝታ በዚህ ቀን ዐርፋለች::

✞✞✞ አምላከ ቅዱሳን ጸጋውን: ክብሩን አይንሳን:: ከወዳጆቹ በረከትም እንደ ቸርነቱ ያድለን::

✞✞✞ መስከረም 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘአርማርያ
2.ቅዱስ ቂርቆስ ገዳማዊ
3.ቅድስት ሮማነ ወርቅ
4.ቅዱስ ዕጸ መስቀል

++"+ ጻድቃን ጮሁ: እግዚአብሔርም ሰማቸው::
ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው::
እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው::
መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል::
የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው::
እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል::
እግዚአብሔር አጥንቶቻቸውን ሁሉ ይጠብቃል:: +"+ (መዝ. 33:17)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

Forwarded from ዝክረ ቅዱሳን zikre kidusan (ɴᴀᴛɴᴀᴇʟ)
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ መስከረም 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞✞✞

+*" ቅዱስጐርጐርዮስ ዘአርማንያ "°+

✞✞✞ ይህ ቅዱስ አባት ከሰማዕታት: ከጻድቃን: ከሊቃውንትና ከዻዻሳት ዝርዝር
ውስጥ ይገኛል:: በቤተ ክርስቲያንም ዓበይትተጽፎ
ከሚባሉ አበው አንዱ ነው:: ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሮማዊ ሲሆን ከክርስቲያን
ወላጆቹ የተወለደው በዘመነ ሰማዕታት (በ3ኛው መቶ
ክ/ዘመን) ነው::

+አበው በትውፊት እንደ ነገሩን ከሆነ ቅዱሱ የታላቁዋ ሰማዕት ቅድስት
አርሴማ ትልቅ ወንድም ነው:: በዜና ሰማዕታት
እንደሚገኘው በዚያ የመከራ ዘመን ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሦስት ኃላፊነቶች
ነበሩበት:-

1.ቅድስት አርሴማን ጨምሮ ደናግሉን ማጽናት
2.ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ ማጥናት
3.የሚመጣውን መከራ ለመቀበል ራሱን ማዘጋጀት::

+ቅዱሱ 3ቱንም ኃላፊነቶች በሚገባ በመወጣቱ ከራሱ አልፎ ለሌሎቹ አርአያ
መሆን ቻለ:: ያቺን ንጽሕት አርበኛ ቅድስት
አርሴማንም አጽንቶ የደናግሉ መሪ አደረጋት:: መከራው በጣም ገፍቶ እስከበመልኩዋ
መጣበት ጊዜ ድረስ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ
ሆነው ይጸልዩ: ይጾሙ: ገዳማዊ ሥራንም ይሠሩ ነበር::

+ለዚህም ነው ቅድስት አርሴማና ቅዱስ ጐርጐርዮስ ጻድቃን የምንላቸው::
በኋላ ግን ማሕደረ ሰይጣን ዲዮቅልጢያኖስ
ተማርኮ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ በማለቱ ቅዱስ ጐርጐርዮስበጸሎት ድንግሏን
አርሴማን ጨምሮ ክርስቲያኖችን ይዞ ወደ አርማንያ
ተሰደደ::

+በአርማንያም በአንድ ገዳም ውስጥ ተደብቀው በጾምና ለጥቂት
ጊዜ ቆዩ: ነገር ግን ረሃብ ፈጃቸው:: የሚላስ
የሚቀመስ ነገር በአካባቢው ባለ መኖሩ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወደ ከተማ
ለመውጣት ተገደደ::

+በዚያም በድርጣድስ ቤተ መንግስት ውስጥ ባርነት ተቀጠረ:: በሚያገኛት
ገንዘብም ወገኖቹን ይረዳ ነበር:: መከራው ግንእኔ
አለቀቃቸውም:: ርጉም ዲዮቅልጢያኖስ ቅዱሳኑ ወደ አርማንያ መሔዳቸውን
ስለ ሰማ ይዞ እንዲልክለት ድርጣድስን ላከው::

+ድርጣድስ ግን ቅድስት አርሴማን ባያት ጊዜ ከውበቷ የተነሳ መታገስ
ባለመቻሉ "ካላገባሁሽ" አላት:: ድንግሊቱ ግን "
የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ: አይሆንም" አለችው:: ሊያስፈራራት ሞከረ:: ዐይኗ እያየ ደናግሉን ጨፈጨፋቸው::

+አልሳካልህ ቢለው በአደባባይ በግድ ሊያገባት ቢሞክር እጁን ጠምዝዛ
በሰው ሁሉ ፊት መሬት ላይ ጣለችው:: እጅግ ስላፈረ
አስገረፋት: አሰቃያት: ዐይኗንም አወጣ:: በመጨረሻም አንገቷን አስቆርጦ
ከሰማዕታቱ ጋር ተራራ ላይ ጣላት::

+ወዲያው ደግሞ የቅዱስ ጐርጐርዮስ ማንነቱ በመታወቁ ይዘው
እስኪያልቅ ገረፉት:: በእሳትም አቃጠሉት:: በብዙሽማግሌ
ስቃይም አሰቃዩት::

+በመጨረሻ ግን ከነ ሕይወቱ እንዲቀበር ተወሰነበት:: ወደ መጸዳጃ ቤት
ወስደውም ከነ ሕይወቱ ቀበሩት:: ነገር ግን
የእግዚአብሔር መልአክ ወርዶ መተንፈሻ ቀዳዳን ሠራለት:: አንዲት
ክርስቲያንም በዚያች ቀዳዳ ቂጣ እየጣለችለት ለ15
ዓመታት ተቀብሮ ኖረ::

+አካሉና አፈሩ ተጣበቀ:: እርሱ ግን ፈጣሪውን እያመሰገነ ቆየ:: ከነገርየንጉሡ ሁሉ በኋላ ድርጣድስና
ባለሟሎቹ ለአደን
በሔዱበት ርኩስ መንፈስ ወደ አውሬነት (እሪያነት) ቀየራቸው::

+የንጉሡ እንስሳ /አውሬ መሆን በአርማንያ ታላቅ ድንጋጤን ፈጠረ::
እህት ስታለቅስ በራዕይ "ለእመ ኢያዕረግምዎ
ለጐርጐርዮስ አልብክሙ ድኂን-ጐርጐርዮስን ከተቀበረበት ካላወጣችሁት
አትድኑም" አላቸው:: ወዲያውም በዚያች ሽማግሌ መሪነት
ቆፍረው አወጡት::

+አካሉንም እግዚአብሔር መለሰለት:: ቅዱሱ እንደ ወጣ ዕረፍትን አልፈለገም::
ለ15 ዓመታት ቀባሪ አጥቶ የተበተነውን
የቅድስት አርሴማንና የሰማዕታቱን አጽም ሰብስቦ በክብር አኖረው::
ድርጣድስና ባለሟሎቹንም ወደ በርሃ ሒዶ ፈወሳቸው::

+ወደ ሰውነትም መልሶ መላ አርማንያን ወደ ክርስትና መለሰ:: የንጉሡን እግር ግን የአውሬ አድርጐት ቀርቷል:: በመጨረሻም
ቅዱስ ጐርጐርዮስ የአርማንያ ሊቀ ዻዻሳት ሆኖ ተሹሞ ብዙ መጻሕፍትን
ደረሰ:: ከ318ቱ ሊቃውንትም አንዱ ሆኖ ተቆጠረ::
ዕረፍቱ ታሕሳስ 15 ቀን ሲሆን ዛሬ ከተቀበረበት የወጣበት ነው::

+" ቅዱስ ቂርቆስ ገዳማዊ "+

+ቅዱሱ የ6ኛው መቶ ክ/ዘመን ጻድቅ ሲሆን በዓለም ከመናፍቃን: በገዳም
ደግሞ ከአጋንንት ብዙ መከራን ተቀብሏል:: በወቅቱ
መለካውያን (የአሁኖቹ ካቶሊኮችና ምስራቅ ኦርቶዶክሶች) አባቶችን
ያሳድዱ ነበር:: ልክ 9ኙ ቅዱሳን በዚህ
ምክንያት ወደ ኢትዮዽያ እንደመጡት ቅዱስ ቂርቆስም ወደ ግብጽ በርሃ ከእርሷ ተሰደደ::

+በበርሃው ውሃም ሆነ ዛፍ ባለመኖሩ በረሃብና በጥም በመሰቃየቱ ወደ ፈጣሪ
ለመነ:: ጌታም አንዲት አጋዘን ልኮለት
ወተትን አልቦ ጠጣ:: እስከ ሕይወቱ ፍጻሜም ምግቡ ይሔው የአጋዘን ወተት
ነበር:: በዚህ ምክንያት ይሔው ዛሬም ድረስ "
ቅዱስ ቂርቆስ ገዳማዊ ዘሲሳዩ ሐሊበ ቶራ" እየተባለ ይጠራል::

+በበርሃው ውስጥ በኖረባቸው ዘመናትም አንድም ሰው አይቶ ካለማወቁስትሆን
ባለፈ አጋንንት በገሃድ እየመጡ ያሰቃዩት ነበር::
ቅዱሱ ግን በትእግስት ኑሮ በዚህች ቀን ሲያርፍ ብዙ ተአምራት በበዓቱ
ውስጥ ተገልጠዋል:: ይህንን ያዩት ደግሞ ከዻዻሱ
ዘንድ ተልከው የቀበሩት አበው ናቸው::

+" ቅድስት ሮማነ ወርቅ "+

+ይህቺ ቅድስት እናት ደግሞ ኢትዮዽያዊት ናት:: የነገሥታቱ ልጅ አባቷ
አፄ ናዖድ: እናቷ ደግሞ እሌኒ /ወለተ
ማርያም ይባላሉ:: ወንድሟ ደግሞ አፄ ልብነ ድንግል ይባላሉ::

+በቤተ መንግስት ውስጥ ብታድግም መንፈሳዊነቷ የገዳም ያህል ነበር::
ከተባረከ ትዳሯም ቅዱስ ላዕከ ማርያምን አፍርታለች::
አብያተ ክርስቲያናትን ከማነጽ ባለፈ የነዳያን እናትም ነበረች:: በክርስትናዋ
ፈጣሪዋን ደስ አሰኝታ በዚህ ቀን ዐርፋለች::

✞✞✞ አምላከ ቅዱሳን ጸጋውን: ክብሩን አይንሳን:: ከወዳጆቹ በረከትም እንደ ቸርነቱ ያድለን::

✞✞✞ መስከረም 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘአርማርያ
2.ቅዱስ ቂርቆስ ገዳማዊ
3.ቅድስት ሮማነ ወርቅ
4.ቅዱስ ዕጸ መስቀል

++"+ ጻድቃን ጮሁ: እግዚአብሔርም ሰማቸው::
ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው::
እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው::
መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል::
የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው::
እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል::
እግዚአብሔር አጥንቶቻቸውን ሁሉ ይጠብቃል:: +"+ (መዝ. 33:17)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>


>>Click here to continue<<

ዘተዋሕዶ - zetewahedo




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)