TG Telegram Group & Channel
ውብ ታሪኮች ® | United States America (US)
Create: Update:

ወረዱ። በየራሳቸው ኮድ እየተነጋገሩ ቀስ በቀስ ቤቱን ከበቡት።

ቤቱን የመቆርቆር ተራው የሙክታር ነበር።
ሙሉ ቀን መብራት ስላልነበረ ፀሀይ ስራዋን ስታገባድድ የሚቀበላት ባለመኖሩ ጨለማ ሆኗል። ከሌሎች ቤቶች ነጠል ብሎ ወደሚገኘውና ግቢ ወደሌለው በር አመራ።
ቆረቆረ መልስ የለም።
ደግሞ ቆረቆረ መልስ የለም።በተደጋጋሚ ቢቆረቁርም መልስ አላገኘም።

ሁኔታውን የሚከታተሉት ፖሊሶች ወደ ቤቱ አመሩ። እርስ በርስ ከተነጋገሩ በኋላ በሩን ገነጠሉት። ብቅ ያለ ሰው የለም፤ የሚጮህ ሰው የለም፤ ጸጥ ያለ ነው። ሙክታር ዘወር ሲል ኸውለት መኪናው አጠገብ እየሰገደች ተመለከተ። እሱም በፍጥነት ሄደ።

የመጀመሪያው ፖሊስ ጥይቱን ደግኖ በጥንቃቄ ገባ። ቤቱን ሲቃኝ በአንደኛው ጥግ ሻማ በርቷል። ካጠገቡ ሲሃም ወንበር ላይ ተጠፍራ ታስራለች። ቀሚሷ እስከ ባቷ ተገልጦ አየ። ሲጠጋት በአይኗ ምልክት ሰጠችው። ሲዞር በመስኮቱ ዘለው ማምለጣቸውን አወቀ።

ፖሊሱ በሲሃም አለባበስ ምራቁን ውጦ እራሱን ለመቀጣጠር እየሞከረ በቅድሚያ እጇን ሲፈታት ቶሎ ብላ ቀሚሷን ዝቅ አደረችው። ፕላስተሩን ከአፏ ላይ አላቃ ቤቱን ለቅሶ በለቅሶ ስታደርገው አባቷ ተንደርድረው ገቡ።

አባቷ እቅፍ አድርገዋት አለቀሱ። እጇን፣ ፊቷን እየደባበሳት ተያይዘው አነቡ።
" አንድ የምመካባትን ልጄን ጉድ ሰሩኝ" እያሉ እንደ ህፃን አለቀሱ። ለቅሷቸው አላልቅ ያላቸው ፖሊሶች ዝም ካስባሏቸው በኋላ አረጋጓቸው።

" ምን አደረጉሽ ልጄ?" አሏት የጆቿን መቆሳሰል ተመልክተው እያሻሹላት።
" ምንም አላደረጉኝም" አለች በደከመ ድምፅ ለቅሶው መልሶ እየጀመራት።

" ኤች አይ ቪ ማለት ምን እንደሆነ ዛሬ በተግባር ታይዋለሽ። ቁርኝታችሁን ትጀምራላችሁ። መብራት ይምጣና ስልካችንን ቻርጅ አድርገን ለአባትሽ በቅድሚያ ደውለን ብር ታስመጪዋለሽ እምቢ ካሉ ቫይረሱ በደማቸው ካሉ እህት ወንድሞችሽ ጋር አደባልቀን እንልክሻለን። " ያሏት ትዝ አላት።

" አላህ ወዶኝ መብራት ያለመኖሩ ነው እንጂ አባዬ ዛሬ ጉድ ሁኜ ነበር!" ብላ ተንሰቅስቃ አለቀሰች። ከአባቷ ብር ቢቀበሉም እንደማይለቋት አስታውሳ።

በሴትነቷ የቀለዱባት፣ ያሰቃዩዋትና የደበደቧት፣ ስሜቱ እየተሰማት ሲመጣ መናገር ደከማት። ሰውነቷ ዛለ። አባቷ ክንድ ላይ እንዳለች በሰመመን ተኛች።

ሙክታርም ኸውለትም መግሪብ ሶላትን ጨርሰው መጥተው ሲያፅናኖአትም አልተሰማትም።

በዚህ መሀል ኸውለት የደወለችለት ኢልያስ በኩንትራት ታክሲ መጣ። ሲገባ ሲሃም የአባቷ ክንድ ላይ ገደፍ ብላ ተመለከተ።
" ደህና ነች?" አለው ሙክታርን ድንጋጤው ሳይለቀው
" አልሃምዱሊላህ ጥቂት ድካም እንጂ ደህና ናት።"
" አይዞህ ተረጋጋ!" አለው እያቀፈው።
" እሽ ሙክታርዬ።" አለው በልቡ አላህን እያመሰገነ።
" ምንድን ነው የተፈጠረው?"
" ኸውለት የነገረችህ ነው አዲስ ነገር የለም"
" ግን ምንም አላደረጓትም?"
" ምንም አላደረጓትም። አላህ ደርሶላታል።"
" ሂጄ ልጠይቃት?" አለው ትንሽ ቆየት ብሎ
" ባትሄድ ጥሩ ነው።"
" ለምን?"
" ትንስ ስለደከማት አታወራህም። እኛንም በደንብ አላወራችንም።" አለው።

የአባቷ እቅፍ ውስጥ ያለችው ሲሃም ወደ በሩ ስትዞር ኢልያስን አየችው። የተሳሰረው ፊቷ ለቀቅ አደረጋት፣ የዛለው ሰውነቷ በረታ፣ እንባ መንታ መንታ ሆኖ በአይኗ ይወርድ ጀመር።

አይኗ ተስለመለመ፣ ከንፈሯ ተንቀጠቀጠ፣ እንባዋ ፊቷን እያሞቀው መውረዱን ቀጠለ። ውስጧ ተንተከተከ።

" ኢልያስዬ ዛሬ አጥቼህ ነበር። ሁለት ሞት ሙቼ ነበር።" እያለች በሆዷ እንደገና ተንሰቅስቃ ማልቀስ ጀመረች።
" በስሜት ለውጧ ውስጡ የተነካው ኢልያስም የእምባዋ መውረድ ሩህሩህ ልቡን ከድንጋጤ ወደ ሀዘን ለወጠው። አይኑ እምባ ሞላ። ዘወር ብሎ የአይኑን ጫፎች ሲጠርግ ሲሃም አየችው። ለቅሶውን ስታይ ስላላስቻላት ውስጧን እምቅ አድርጋ አለቀሰች። የሱ እምባ በመቶ ተባዝቶ በሷ ይወጣ ይመስል እየፈነቀላት ይወርድ ጀመር።

አባቷ ትንሽ ካረጓጓት በኋላ" ቶሎ ሆስፒታል ሂደን ካልተሻላት በአፋጣኝ ወደ ታይላንድ እንሄዳለን።" እያሏት በገመዱ እስራት የተነሳ መራመድ ባለመቻሏ በእጃቸው ተሸክመዋት ወጡ።

" አላህ ያሽርሽ" አላት ኢልያስ በአጠገቡ ስታልፍ።
ውስጥን ሰርስሮ በሚገባ እይታ ውጭ ምንም አላላቸውም።

ሲሃም በአባቷ መኪና፣ ነገ የሚመረቀው ኢልያስ ከኸውለትና ከሙክታር ጋር በላዳው ታክሲ፣ የራህማ ወንድምና ጓደኛው ደግሞ በፖሊሶቹ መኪና ወደየተለያየ አቅጣጫ ሄዱ።

ኸውለት ተኝታ እያሰላሰለች ነው። ታወጣለች፤ ታወርዳለች፤ ትጥላለች፤ ታነሳለች፤ ከአንድ ጉኗ ወደ ሌላ ጉኗ ትዘዋወራለች።
ቅድም ሙክታር ያላት ትዝ አላት።
ከላዳው ታክሲ ወርደው ወደየ ቤታቸው ሊገቡ ሲሉ
" ሙክታር የቅድሙን አትነግረኝም?" አለችው።
ያለምንም መንደርደሪያና ማቅማማት " ዘምዘም ውሃ የጠጣሁት #ሶስተኛ ኒያየ አንቺን ሊድረኝ ብየ ነው። ደህና እደሪ።" ብሏት በሩን ዘጋው።

ባለችበት ደርቃ ቀርታ ነበር፤ ወደምትራመድበት ጠፋት፤ የሲሃም ሀስብ ከላይዋ ላይ ጠፍቶ በራሷ ሀሳብ ተተካ፤ ድብልቅልቅ ያለ ለመለየት የሚከብድ ውዥንብር ተፈጠረባት። እሽ አይባል ነገር እምቢ አይባል ነገር።

በተኛበት የሲሃም እገታን ከቁብ ሳትቆጥር መብሰልሰሏን ቀጠለች። ተሰምቷት የማያውቀው እንቅልፍ የማጣት ስሜት ጀመራት።
ስለ ሙክታር ስታወጣ ስታወርድ ቆየች።

" እንዴት ደፍሮ አሰበኝ? ሺ ጊዜ ቢለወጥ እንዴት የሱ አይነት ሰው ለኔ ባል ይሆናል? በዚህ ህይወት ላይ ያለፈ ሰው መከታ፤ የልጅ አባት፤ የጀነት መንደርደሪያ እንዴት ይሆናል? ባል ቀላል ነገር ነው እንዴ?"

" አኡዙቢላሂ ሚነሸይጧኒ ረጂም! ምን ነካኝ? ሸይጧን ነው እንዲህ መጥፎ መጥፎውን የሚያሳስበኝ።" ወዳልተኛችበት ጎኗ ዞረች።
" ለነገሩ ሰው እንደሆነ ያጠፋል። ምን አዲ ነገር አለው? አይደለም እሱ ከሱ በላይ ናቸው የሚባሉትም ያጠፋሉ። ምርጡ ግን ከጥፋቱ ተመላሹ ነው። እሱ ደግሞ መመለስ ብቻ ሳይሆን ጠንካራ መመለስ ላይ ነው ያለው።ሱናን በራሱ ላይ አምጥቷል።"
መዟዟሯን ቀጥላለች።

" ከጨዋታው አንፃር እድሜ ልኬን ተደስቼ እንደምኖር ባውቅም ዋናው ግን ዲን ነው። በዲን በኩል ደግሞ ሞት አፋፍ ላይ ሆኖ ሆስፒታል ከመሄድ ይልቅ ዑምራን ከመመኘት በላይ ዲነኝነት የለም።"

" አኽላቁ፣ አክብሮቱና ክድሚያው ሁሉ ተስተካክሏል። አይኑም መሰበር ጀምሯል። ከምንም በላይ ደግሞ ቁርዐን ሀፍዞ አላህ ትልቅ ደረጃ ከሚሰጣቸው ሰዎች ሊሆን ነው። እኔንም ሊያሳፍዘኝ ይችላል። ይሄ ደግሞ በህልሜም በእውኔም አስቤው የማላውቀው እድል ነው።"

" በዚያም አለ በዚህ እሱን እንቢ ለማለት ሸርጥ የለኝም። እሽታም ግን አስቸጋሪ ነው። የሰፈር ሰው ግን ምን ይለኛል?"

" ምን አባቴ ላድርግ?"

በሃሳብ ባህር እየቀዘፈች መቆም በሌለባት እየቆመች መሄድ በሌለባት እየሄደች የወደፊት ህይወቷን አጋር መዳረሻዋ ላይ መረጠችው። ከአድካሚ ጉዞ፣ እልህ አስጨራሽ ትግልና ለውሳኔ አስቸጋሪ ከሆነ እንቅልፍ ማጣት በኋላ ለእምቢታዋና እሽታዋ ተቀራራቢ ነጥብ የሰጠቻቸው ቢሆንም 51 ለ 49 ሁነውባት ሀሳቧ ያዘነበለበትን መረጠች።

በመጨረሻም #አዳበ ነውም አድርጋ ተኛች....

ክፍል-47 ይቀጥላል #ሼር / እንወዳችኋለን❤️

ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡ @WubTarikoch
ለሀሳብና አስተያየት፡ @WubTarikoch_bot

ወረዱ። በየራሳቸው ኮድ እየተነጋገሩ ቀስ በቀስ ቤቱን ከበቡት።

ቤቱን የመቆርቆር ተራው የሙክታር ነበር።
ሙሉ ቀን መብራት ስላልነበረ ፀሀይ ስራዋን ስታገባድድ የሚቀበላት ባለመኖሩ ጨለማ ሆኗል። ከሌሎች ቤቶች ነጠል ብሎ ወደሚገኘውና ግቢ ወደሌለው በር አመራ።
ቆረቆረ መልስ የለም።
ደግሞ ቆረቆረ መልስ የለም።በተደጋጋሚ ቢቆረቁርም መልስ አላገኘም።

ሁኔታውን የሚከታተሉት ፖሊሶች ወደ ቤቱ አመሩ። እርስ በርስ ከተነጋገሩ በኋላ በሩን ገነጠሉት። ብቅ ያለ ሰው የለም፤ የሚጮህ ሰው የለም፤ ጸጥ ያለ ነው። ሙክታር ዘወር ሲል ኸውለት መኪናው አጠገብ እየሰገደች ተመለከተ። እሱም በፍጥነት ሄደ።

የመጀመሪያው ፖሊስ ጥይቱን ደግኖ በጥንቃቄ ገባ። ቤቱን ሲቃኝ በአንደኛው ጥግ ሻማ በርቷል። ካጠገቡ ሲሃም ወንበር ላይ ተጠፍራ ታስራለች። ቀሚሷ እስከ ባቷ ተገልጦ አየ። ሲጠጋት በአይኗ ምልክት ሰጠችው። ሲዞር በመስኮቱ ዘለው ማምለጣቸውን አወቀ።

ፖሊሱ በሲሃም አለባበስ ምራቁን ውጦ እራሱን ለመቀጣጠር እየሞከረ በቅድሚያ እጇን ሲፈታት ቶሎ ብላ ቀሚሷን ዝቅ አደረችው። ፕላስተሩን ከአፏ ላይ አላቃ ቤቱን ለቅሶ በለቅሶ ስታደርገው አባቷ ተንደርድረው ገቡ።

አባቷ እቅፍ አድርገዋት አለቀሱ። እጇን፣ ፊቷን እየደባበሳት ተያይዘው አነቡ።
" አንድ የምመካባትን ልጄን ጉድ ሰሩኝ" እያሉ እንደ ህፃን አለቀሱ። ለቅሷቸው አላልቅ ያላቸው ፖሊሶች ዝም ካስባሏቸው በኋላ አረጋጓቸው።

" ምን አደረጉሽ ልጄ?" አሏት የጆቿን መቆሳሰል ተመልክተው እያሻሹላት።
" ምንም አላደረጉኝም" አለች በደከመ ድምፅ ለቅሶው መልሶ እየጀመራት።

" ኤች አይ ቪ ማለት ምን እንደሆነ ዛሬ በተግባር ታይዋለሽ። ቁርኝታችሁን ትጀምራላችሁ። መብራት ይምጣና ስልካችንን ቻርጅ አድርገን ለአባትሽ በቅድሚያ ደውለን ብር ታስመጪዋለሽ እምቢ ካሉ ቫይረሱ በደማቸው ካሉ እህት ወንድሞችሽ ጋር አደባልቀን እንልክሻለን። " ያሏት ትዝ አላት።

" አላህ ወዶኝ መብራት ያለመኖሩ ነው እንጂ አባዬ ዛሬ ጉድ ሁኜ ነበር!" ብላ ተንሰቅስቃ አለቀሰች። ከአባቷ ብር ቢቀበሉም እንደማይለቋት አስታውሳ።

በሴትነቷ የቀለዱባት፣ ያሰቃዩዋትና የደበደቧት፣ ስሜቱ እየተሰማት ሲመጣ መናገር ደከማት። ሰውነቷ ዛለ። አባቷ ክንድ ላይ እንዳለች በሰመመን ተኛች።

ሙክታርም ኸውለትም መግሪብ ሶላትን ጨርሰው መጥተው ሲያፅናኖአትም አልተሰማትም።

በዚህ መሀል ኸውለት የደወለችለት ኢልያስ በኩንትራት ታክሲ መጣ። ሲገባ ሲሃም የአባቷ ክንድ ላይ ገደፍ ብላ ተመለከተ።
" ደህና ነች?" አለው ሙክታርን ድንጋጤው ሳይለቀው
" አልሃምዱሊላህ ጥቂት ድካም እንጂ ደህና ናት።"
" አይዞህ ተረጋጋ!" አለው እያቀፈው።
" እሽ ሙክታርዬ።" አለው በልቡ አላህን እያመሰገነ።
" ምንድን ነው የተፈጠረው?"
" ኸውለት የነገረችህ ነው አዲስ ነገር የለም"
" ግን ምንም አላደረጓትም?"
" ምንም አላደረጓትም። አላህ ደርሶላታል።"
" ሂጄ ልጠይቃት?" አለው ትንሽ ቆየት ብሎ
" ባትሄድ ጥሩ ነው።"
" ለምን?"
" ትንስ ስለደከማት አታወራህም። እኛንም በደንብ አላወራችንም።" አለው።

የአባቷ እቅፍ ውስጥ ያለችው ሲሃም ወደ በሩ ስትዞር ኢልያስን አየችው። የተሳሰረው ፊቷ ለቀቅ አደረጋት፣ የዛለው ሰውነቷ በረታ፣ እንባ መንታ መንታ ሆኖ በአይኗ ይወርድ ጀመር።

አይኗ ተስለመለመ፣ ከንፈሯ ተንቀጠቀጠ፣ እንባዋ ፊቷን እያሞቀው መውረዱን ቀጠለ። ውስጧ ተንተከተከ።

" ኢልያስዬ ዛሬ አጥቼህ ነበር። ሁለት ሞት ሙቼ ነበር።" እያለች በሆዷ እንደገና ተንሰቅስቃ ማልቀስ ጀመረች።
" በስሜት ለውጧ ውስጡ የተነካው ኢልያስም የእምባዋ መውረድ ሩህሩህ ልቡን ከድንጋጤ ወደ ሀዘን ለወጠው። አይኑ እምባ ሞላ። ዘወር ብሎ የአይኑን ጫፎች ሲጠርግ ሲሃም አየችው። ለቅሶውን ስታይ ስላላስቻላት ውስጧን እምቅ አድርጋ አለቀሰች። የሱ እምባ በመቶ ተባዝቶ በሷ ይወጣ ይመስል እየፈነቀላት ይወርድ ጀመር።

አባቷ ትንሽ ካረጓጓት በኋላ" ቶሎ ሆስፒታል ሂደን ካልተሻላት በአፋጣኝ ወደ ታይላንድ እንሄዳለን።" እያሏት በገመዱ እስራት የተነሳ መራመድ ባለመቻሏ በእጃቸው ተሸክመዋት ወጡ።

" አላህ ያሽርሽ" አላት ኢልያስ በአጠገቡ ስታልፍ።
ውስጥን ሰርስሮ በሚገባ እይታ ውጭ ምንም አላላቸውም።

ሲሃም በአባቷ መኪና፣ ነገ የሚመረቀው ኢልያስ ከኸውለትና ከሙክታር ጋር በላዳው ታክሲ፣ የራህማ ወንድምና ጓደኛው ደግሞ በፖሊሶቹ መኪና ወደየተለያየ አቅጣጫ ሄዱ።

ኸውለት ተኝታ እያሰላሰለች ነው። ታወጣለች፤ ታወርዳለች፤ ትጥላለች፤ ታነሳለች፤ ከአንድ ጉኗ ወደ ሌላ ጉኗ ትዘዋወራለች።
ቅድም ሙክታር ያላት ትዝ አላት።
ከላዳው ታክሲ ወርደው ወደየ ቤታቸው ሊገቡ ሲሉ
" ሙክታር የቅድሙን አትነግረኝም?" አለችው።
ያለምንም መንደርደሪያና ማቅማማት " ዘምዘም ውሃ የጠጣሁት #ሶስተኛ ኒያየ አንቺን ሊድረኝ ብየ ነው። ደህና እደሪ።" ብሏት በሩን ዘጋው።

ባለችበት ደርቃ ቀርታ ነበር፤ ወደምትራመድበት ጠፋት፤ የሲሃም ሀስብ ከላይዋ ላይ ጠፍቶ በራሷ ሀሳብ ተተካ፤ ድብልቅልቅ ያለ ለመለየት የሚከብድ ውዥንብር ተፈጠረባት። እሽ አይባል ነገር እምቢ አይባል ነገር።

በተኛበት የሲሃም እገታን ከቁብ ሳትቆጥር መብሰልሰሏን ቀጠለች። ተሰምቷት የማያውቀው እንቅልፍ የማጣት ስሜት ጀመራት።
ስለ ሙክታር ስታወጣ ስታወርድ ቆየች።

" እንዴት ደፍሮ አሰበኝ? ሺ ጊዜ ቢለወጥ እንዴት የሱ አይነት ሰው ለኔ ባል ይሆናል? በዚህ ህይወት ላይ ያለፈ ሰው መከታ፤ የልጅ አባት፤ የጀነት መንደርደሪያ እንዴት ይሆናል? ባል ቀላል ነገር ነው እንዴ?"

" አኡዙቢላሂ ሚነሸይጧኒ ረጂም! ምን ነካኝ? ሸይጧን ነው እንዲህ መጥፎ መጥፎውን የሚያሳስበኝ።" ወዳልተኛችበት ጎኗ ዞረች።
" ለነገሩ ሰው እንደሆነ ያጠፋል። ምን አዲ ነገር አለው? አይደለም እሱ ከሱ በላይ ናቸው የሚባሉትም ያጠፋሉ። ምርጡ ግን ከጥፋቱ ተመላሹ ነው። እሱ ደግሞ መመለስ ብቻ ሳይሆን ጠንካራ መመለስ ላይ ነው ያለው።ሱናን በራሱ ላይ አምጥቷል።"
መዟዟሯን ቀጥላለች።

" ከጨዋታው አንፃር እድሜ ልኬን ተደስቼ እንደምኖር ባውቅም ዋናው ግን ዲን ነው። በዲን በኩል ደግሞ ሞት አፋፍ ላይ ሆኖ ሆስፒታል ከመሄድ ይልቅ ዑምራን ከመመኘት በላይ ዲነኝነት የለም።"

" አኽላቁ፣ አክብሮቱና ክድሚያው ሁሉ ተስተካክሏል። አይኑም መሰበር ጀምሯል። ከምንም በላይ ደግሞ ቁርዐን ሀፍዞ አላህ ትልቅ ደረጃ ከሚሰጣቸው ሰዎች ሊሆን ነው። እኔንም ሊያሳፍዘኝ ይችላል። ይሄ ደግሞ በህልሜም በእውኔም አስቤው የማላውቀው እድል ነው።"

" በዚያም አለ በዚህ እሱን እንቢ ለማለት ሸርጥ የለኝም። እሽታም ግን አስቸጋሪ ነው። የሰፈር ሰው ግን ምን ይለኛል?"

" ምን አባቴ ላድርግ?"

በሃሳብ ባህር እየቀዘፈች መቆም በሌለባት እየቆመች መሄድ በሌለባት እየሄደች የወደፊት ህይወቷን አጋር መዳረሻዋ ላይ መረጠችው። ከአድካሚ ጉዞ፣ እልህ አስጨራሽ ትግልና ለውሳኔ አስቸጋሪ ከሆነ እንቅልፍ ማጣት በኋላ ለእምቢታዋና እሽታዋ ተቀራራቢ ነጥብ የሰጠቻቸው ቢሆንም 51 ለ 49 ሁነውባት ሀሳቧ ያዘነበለበትን መረጠች።

በመጨረሻም #አዳበ ነውም አድርጋ ተኛች....

ክፍል-47 ይቀጥላል #ሼር / እንወዳችኋለን❤️

ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡ @WubTarikoch
ለሀሳብና አስተያየት፡ @WubTarikoch_bot


>>Click here to continue<<

ውብ ታሪኮች ®




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)