TG Telegram Group & Channel
ወሒድ የንጽጽር ማኅደር | United States America (US)
Create: Update:

ሙሥሊም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

15፥2 እነዚያ የካዱት በትንሣኤ ቀን ሙሥሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡ رُّبَمَا يَوَدُّ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْ كَانُوا مُسْلِمِينَ

"ሙሥሊም" مُسْلِم የሚለው ቃል "አሥለመ" أَسْلَمَ ማለትም "ታዘዘ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ታዛዥ" ማለት ነው፥ የሙሥሊም ብዙ ቁጥር ደግሞ "ሙሥሊሙን" مُّسْلِمُون ወይም "ሙሥሊሚን" مُسْلِمِين ሲሆን "ታዛዦች" ማለት ነው፦
21፥108 «ያ ወደ እኔ የሚወረደው፦ “አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው” ማለት ነው፥ ታዲያ እናንተ ፍጹም ታዛዦች ናችሁን» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا يُوحَىٰ إِلَيَّ أَنَّمَا إِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ ۖ فَهَلْ أَنتُم مُّسْلِمُون

እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዛዦች" ለሚለው የገባው ቃል "ሙሥሊሙን" مُّسْلِمُون ሲሆን "ሙሥሊም" مُسْلِم ማለት "አንዱን አምላክ በብቸኝነት የሚያመልክ ወይም የሚታዘዝ" ማለት ነው፥ የፈጠረንን አሏህን በሙፍረዳት እና በሙሐረማት ወይንም በአምስቱ ሙሐከማት ስንታዘዝ ሙሥሊም እንሰኛለን። አምላካችን አሏህ ወደ አደም ኪዳን ሲያወርድ "ሙሥሊሞች" ብሎ ጠራን፦
20፥115 ወደ አደምም ከዚህ በፊት ኪዳንን በእርግጥ አወረድን፡፡ وَلَقَدْ عَهِدْنَا إِلَىٰ آدَمَ مِن قَبْلُ
22፥78 በአላህም ሃይማኖት ተገቢውን ትግል ታገሉ፡፡ እርሱ መርጧችኋል፡፡ በእናንተም ላይ በሃይማኖቱ ውስጥ ምንም ችግር አላደረገባችሁም፡፡ የአባታችሁን የኢብራሂምን ሃይማኖት ተከተሉ፡፡ እርሱ ከዚህ በፊት ሙሥሊሞች ብሎ ሰይሟችኋል፡፡ وَجَاهِدُوا فِي اللَّهِ حَقَّ جِهَادِهِ ۚ هُوَ اجْتَبَاكُمْ وَمَا جَعَلَ عَلَيْكُمْ فِي الدِّينِ مِنْ حَرَجٍ ۚ مِّلَّةَ أَبِيكُمْ إِبْرَاهِيمَ ۚ هُوَ سَمَّاكُمُ الْمُسْلِمِينَ مِن قَبْلُ

ቁርኣን በወረደበት ጊዜ አሏህ፦ "ሚን ቀብሉ" مِن قَبْلُ ማለትም "ከዚህ በፊት" የሚለውን ኢሥሙል መጅሩር የሚጠቁመን ወደ አደም ወሕይን ያወረደበትን ጊዜ ነው፥ በዚያን ጊዜ "ሙስሊሞች" ብሎ ሰይሟል። "እርሱ" የሚለው ተውላጠ ስም "አሏህ" የሚለውን ስም ተክቶ የመጣ ስለሆነ "ሙስሊሞች" ብሎ የሰየመው ኢብራሂም ሳይሆን አሏህ ነው፥ ምክንያቱም ከኢብራሂም በፊት ኑሕ፦ "ከሙሥሊሞች" እንደሆነ ተናግሯል፦
10፥72 «ብትሸሹም አትጎዱኝም፡፡ ከምንዳ ምንንም አልለምናችሁምና፥ ምንዳዬ በአላህ ላይ እንጂ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ከሙሥሊሞች እንድሆንም ታዝዣለሁ፡፡» فَإِن تَوَلَّيْتُمْ فَمَا سَأَلْتُكُم مِّنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَى اللَّهِ ۖ وَأُمِرْتُ أَنْ أَكُونَ مِنَ الْمُسْلِمِينَ

ከኑሕ በኃላ ኢብራሂም ከልጁ ከኢሥማዒል ጋር፦ "ሙሥሊሞች አርገን" ብሎ ዱዓእ አርጓል፦
2፥128 ጌታችን ሆይ! ለአንተ ታዛዦችም አድርገን፡፡ ከዘሮቻችንም ለአንተ ታዛዦች ሕዝቦችን አድርግ፡፡ رَبَّنَا وَاجْعَلْنَا مُسْلِمَيْنِ لَكَ وَمِن ذُرِّيَّتِنَا أُمَّةً مُّسْلِمَةً لَّكَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዛዦች" ለሚለው የገባው ቃል "ሙሥሊማህ" مُّسْلِمَة መሆኑ በራሱ ሙሥሊም ማለት ለአሏህ ታዛዥ መሆኑን ቁልጭ አርጎ አያሳይምን? አሏህ ኢብራሂምን፦ "አሥሊም" أَسْلِمْ ባለው ጊዜ "አሥለምቱ" أَسْلَمْتُ አለው፦
2፥131 ጌታው ለእርሱ ታዘዝ ባለው ጊዜ ለዓለማት ጌታ ታዘዝኩ አለ፡፡ إِذْ قَالَ لَهُ رَبُّهُ أَسْلِمْ ۖ قَالَ أَسْلَمْتُ لِرَبِّ الْعَالَمِينَ

ኢብራሂም ልጆቹን ኢሥማዒልን እና ይስሓቅን እንዲሁ የልጅ ልጁን የዕቁብን በኢሥላም አዘዘ፦
2፥132 በእርሷም ኢብራሂም ልጆቹን አዘዘ፡፡ وَوَصَّىٰ بِهَا إِبْرَاهِيمُ بَنِيهِ

ሙሥሊም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

15፥2 እነዚያ የካዱት በትንሣኤ ቀን ሙሥሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡ رُّبَمَا يَوَدُّ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْ كَانُوا مُسْلِمِينَ

"ሙሥሊም" مُسْلِم የሚለው ቃል "አሥለመ" أَسْلَمَ ማለትም "ታዘዘ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ታዛዥ" ማለት ነው፥ የሙሥሊም ብዙ ቁጥር ደግሞ "ሙሥሊሙን" مُّسْلِمُون ወይም "ሙሥሊሚን" مُسْلِمِين ሲሆን "ታዛዦች" ማለት ነው፦
21፥108 «ያ ወደ እኔ የሚወረደው፦ “አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው” ማለት ነው፥ ታዲያ እናንተ ፍጹም ታዛዦች ናችሁን» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا يُوحَىٰ إِلَيَّ أَنَّمَا إِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ ۖ فَهَلْ أَنتُم مُّسْلِمُون

እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዛዦች" ለሚለው የገባው ቃል "ሙሥሊሙን" مُّسْلِمُون ሲሆን "ሙሥሊም" مُسْلِم ማለት "አንዱን አምላክ በብቸኝነት የሚያመልክ ወይም የሚታዘዝ" ማለት ነው፥ የፈጠረንን አሏህን በሙፍረዳት እና በሙሐረማት ወይንም በአምስቱ ሙሐከማት ስንታዘዝ ሙሥሊም እንሰኛለን። አምላካችን አሏህ ወደ አደም ኪዳን ሲያወርድ "ሙሥሊሞች" ብሎ ጠራን፦
20፥115 ወደ አደምም ከዚህ በፊት ኪዳንን በእርግጥ አወረድን፡፡ وَلَقَدْ عَهِدْنَا إِلَىٰ آدَمَ مِن قَبْلُ
22፥78 በአላህም ሃይማኖት ተገቢውን ትግል ታገሉ፡፡ እርሱ መርጧችኋል፡፡ በእናንተም ላይ በሃይማኖቱ ውስጥ ምንም ችግር አላደረገባችሁም፡፡ የአባታችሁን የኢብራሂምን ሃይማኖት ተከተሉ፡፡ እርሱ ከዚህ በፊት ሙሥሊሞች ብሎ ሰይሟችኋል፡፡ وَجَاهِدُوا فِي اللَّهِ حَقَّ جِهَادِهِ ۚ هُوَ اجْتَبَاكُمْ وَمَا جَعَلَ عَلَيْكُمْ فِي الدِّينِ مِنْ حَرَجٍ ۚ مِّلَّةَ أَبِيكُمْ إِبْرَاهِيمَ ۚ هُوَ سَمَّاكُمُ الْمُسْلِمِينَ مِن قَبْلُ

ቁርኣን በወረደበት ጊዜ አሏህ፦ "ሚን ቀብሉ" مِن قَبْلُ ማለትም "ከዚህ በፊት" የሚለውን ኢሥሙል መጅሩር የሚጠቁመን ወደ አደም ወሕይን ያወረደበትን ጊዜ ነው፥ በዚያን ጊዜ "ሙስሊሞች" ብሎ ሰይሟል። "እርሱ" የሚለው ተውላጠ ስም "አሏህ" የሚለውን ስም ተክቶ የመጣ ስለሆነ "ሙስሊሞች" ብሎ የሰየመው ኢብራሂም ሳይሆን አሏህ ነው፥ ምክንያቱም ከኢብራሂም በፊት ኑሕ፦ "ከሙሥሊሞች" እንደሆነ ተናግሯል፦
10፥72 «ብትሸሹም አትጎዱኝም፡፡ ከምንዳ ምንንም አልለምናችሁምና፥ ምንዳዬ በአላህ ላይ እንጂ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ከሙሥሊሞች እንድሆንም ታዝዣለሁ፡፡» فَإِن تَوَلَّيْتُمْ فَمَا سَأَلْتُكُم مِّنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَى اللَّهِ ۖ وَأُمِرْتُ أَنْ أَكُونَ مِنَ الْمُسْلِمِينَ

ከኑሕ በኃላ ኢብራሂም ከልጁ ከኢሥማዒል ጋር፦ "ሙሥሊሞች አርገን" ብሎ ዱዓእ አርጓል፦
2፥128 ጌታችን ሆይ! ለአንተ ታዛዦችም አድርገን፡፡ ከዘሮቻችንም ለአንተ ታዛዦች ሕዝቦችን አድርግ፡፡ رَبَّنَا وَاجْعَلْنَا مُسْلِمَيْنِ لَكَ وَمِن ذُرِّيَّتِنَا أُمَّةً مُّسْلِمَةً لَّكَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዛዦች" ለሚለው የገባው ቃል "ሙሥሊማህ" مُّسْلِمَة መሆኑ በራሱ ሙሥሊም ማለት ለአሏህ ታዛዥ መሆኑን ቁልጭ አርጎ አያሳይምን? አሏህ ኢብራሂምን፦ "አሥሊም" أَسْلِمْ ባለው ጊዜ "አሥለምቱ" أَسْلَمْتُ አለው፦
2፥131 ጌታው ለእርሱ ታዘዝ ባለው ጊዜ ለዓለማት ጌታ ታዘዝኩ አለ፡፡ إِذْ قَالَ لَهُ رَبُّهُ أَسْلِمْ ۖ قَالَ أَسْلَمْتُ لِرَبِّ الْعَالَمِينَ

ኢብራሂም ልጆቹን ኢሥማዒልን እና ይስሓቅን እንዲሁ የልጅ ልጁን የዕቁብን በኢሥላም አዘዘ፦
2፥132 በእርሷም ኢብራሂም ልጆቹን አዘዘ፡፡ وَوَصَّىٰ بِهَا إِبْرَاهِيمُ بَنِيهِ


>>Click here to continue<<

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)