TG Telegram Group & Channel
ወሒድ የንጽጽር ማኅደር | United States America (US)
Create: Update:

ኢሥቲቃማህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

11፥112 እንደ ታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ ከአንተ ጋር ያመኑትም ቀጥ ይበሉ፡፡ فَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ وَمَن تَابَ مَعَكَ

በኢሥላም ነገረ-ድኅነት"soteriology" እራሱን የቻለ ትልቅ ነጥብ ሲሆን "ፈላሕ” فَلَّاح ወይም "ነጃህ" نَّجَاة ይባላል፦
40፥41 ወገኖቼም ሆይ! ወደ መዳን የምጠራችሁ ስኾን ወደ እሳት የምትጠሩኝ ስትኾኑ ለእኔ ምን አለኝ? وَيَا قَوْمِ مَا لِي أَدْعُوكُمْ إِلَى النَّجَاةِ وَتَدْعُونَنِي إِلَى النَّارِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "መዳን" ለሚለው የገባው ቃል "ነጃህ" نَّجَاة እንደሆነ ልብ በል! ሰዎችን ወደ ኢሥላም ስንጠራ ከእሳት እንዲድኑ ነው። አምላካችን አሏህ ምሕረት አድርጎ ከአሳማሚ ቅጣት የሚያድነን ንስሓ ስንገባ፣ ስናምን፣ መልካም ሥራ ሥንሠራ እና ስንጸና ነው፦
20፥82 እኔም ለተጸጸተ፣ ላመነም፣ መልካምንም ለሠራ፣ ከዚያም ለተመራ ሰው በእርግጥ መሐሪ ነኝ። وَإِنِّي لَغَفَّارٌ لِّمَن تَابَ وَآمَنَ وَعَمِلَ صَالِحًا ثُمَّ اهْتَدَىٰ

"ለተጸጸተ" ሲል ንስሓን፣ "ላመነ" ሲል ኢማንን፣ "መልካምን ለሠራ" ሲል ዐሚሉ ሷሊሓትን፣ "ለተመራ" ሲል ኢሥቲቃማህን ያመለክታል፥ ኢሥቲቃማህ በተጸጸተበት ንስሓ፣ ባመነበት ኢማን እና በምንሠራው መልካም ሥራ መጽናት ነው። "ኢሥቲቃማህ" اِسْتِقَامَة የሚለው ቃል "ኢሥቲቃመ اِسْتَقَامَ ማለትም "ቆመ" ወይም "ጸና" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ጽናት" ማለት ነው፦
42፥15 ለዚህም ድንጋጌ ሰዎችን ጥራ፡፡ እንደታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ فَلِذَٰلِكَ فَادْعُ ۖ وَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ
11፥112 እንደ ታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ ከአንተ ጋር ያመኑትም ቀጥ ይበሉ፡፡ فَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ وَمَن تَابَ مَعَكَ

እነዚህ አንቀጽ ላይ "ቀጥ በል" ለሚለው የገባው ቃል "ኢሥተቂም" اسْتَقِمْ ሲሆን "ጽና" ማለት ነው፥ በቀጥተኛው መንገድ ላይ መጽናት ፍርሃት እና ሐዘን ሳይኖር የጀነት ለመሆን መበሰር ነው፦
46፥13 እነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ያሉ፣ ከዚያም ቀጥ ያሉ በእነርሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም። እነርሱም አያዝኑም፡፡ إِنَّ الَّذِينَ قَالُوا رَبُّنَا اللَّهُ ثُمَّ اسْتَقَامُوا فَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
41፥30 እነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ያሉ ከዚያም ቀጥ ያሉ «አትፍሩ፤ አትዘኑም፤ በዚያችም ተስፋ ቃል ትደረግላችሁ በነበራችሁት ገነት ተበሰሩ» በማለት በእነርሱ ላይ መላእክት ይወርዳሉ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ قَالُوا رَبُّنَا اللَّهُ ثُمَّ اسْتَقَامُوا تَتَنَزَّلُ عَلَيْهِمُ الْمَلَائِكَةُ أَلَّا تَخَافُوا وَلَا تَحْزَنُوا وَأَبْشِرُوا بِالْجَنَّةِ الَّتِي كُنتُمْ تُوعَدُون

እነዚህ አናቅጽ ላይ "ቀጥ ያሉ" ለሚለው ቃል የገባው "ኢሥተቃሙ" اسْتَقَامُوا ሲሆን አምላካችን አሏህ በዲኑል ኢሥላም ለሚጸኑ አማንያን ጀነትን ተስፋ ሰቷቸዋል፦
17፥108 ይላሉም «ጌታችን ጥራት ይገባው! እነሆ የጌታችን ተስፋ ተፈጻሚ ነው፡፡» وَيَقُولُونَ سُبْحَانَ رَبِّنَا إِن كَانَ وَعْدُ رَبِّنَا لَمَفْعُولًا
19፥61 የመኖሪያን ገነቶች ያችን አልረሕማን ለባሮቹ በሩቅ ኾነው ሳሉ ተስፋ ቃል የገባላቸውን ይገባሉ፡፡ እርሱ ተስፋው ተፈጻሚ ነውና። جَنَّاتِ عَدْنٍ الَّتِي وَعَدَ الرَّحْمَـٰنُ عِبَادَهُ بِالْغَيْبِ ۚ إِنَّهُ كَانَ وَعْدُهُ مَأْتِيًّا

ለጽናት ጉልኅ ሚናህ ያለው አሏህን ለመገናኘት ተስፋ ማድረግ ነው፥ ከእዝነቱ ተስፋ መቁረጥ ግን ለጽናት እንቅፋት ነው፦
29፥5 የአላህን መገናኘት ተስፋ የሚያደርግ ሰው ይዘጋጅ፡፡ የአላህ ቀጠሮ በእርግጥ መጪ ነውና፡፡ እርሱም ሰሚው ዐዋቂው ነው፡፡ مَن كَانَ يَرْجُو لِقَاءَ اللَّهِ فَإِنَّ أَجَلَ اللَّهِ لَآتٍ ۚ وَهُوَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ
29፥23 እነዚያም በአላህ አንቀጾችና በመገናኘቱ የካዱ እነዚያ ከእዝነቴ ተስፋን ቆረጡ፡፡ እነዚያም ለእነሱ አሳማሚ ቅጣት አላቸው፡፡ وَالَّذِينَ كَفَرُوا بِآيَاتِ اللَّهِ وَلِقَائِهِ أُولَـٰئِكَ يَئِسُوا مِن رَّحْمَتِي وَأُولَـٰئِكَ لَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ

አምላካችን አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነውና በሰጠን ተስፋ ወደ እርሱ ቀጥ ማለት ለጀነት ይዳርጋል፦
31፥6 እንዲህ በላቸው «እኔ መሰላችሁ ሰው ብቻ ነኝ፡፡ አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው ወደ እርሱም "ቀጥ በሉ" ምሕረትንም ለምኑት» ማለት ወደ እኔ ይወረድልኛል፡፡ ለአጋሪዎቹም ወዮላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا أَنَا بَشَرٌ مِّثْلُكُمْ يُوحَىٰ إِلَيَّ أَنَّمَا إِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ فَاسْتَقِيمُوا إِلَيْهِ وَاسْتَغْفِرُوهُ ۗ وَوَيْلٌ لِّلْمُشْرِكِينَ

አሏህ በዲኑል ኢሥላም ያጽናን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://hottg.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

ኢሥቲቃማህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

11፥112 እንደ ታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ ከአንተ ጋር ያመኑትም ቀጥ ይበሉ፡፡ فَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ وَمَن تَابَ مَعَكَ

በኢሥላም ነገረ-ድኅነት"soteriology" እራሱን የቻለ ትልቅ ነጥብ ሲሆን "ፈላሕ” فَلَّاح ወይም "ነጃህ" نَّجَاة ይባላል፦
40፥41 ወገኖቼም ሆይ! ወደ መዳን የምጠራችሁ ስኾን ወደ እሳት የምትጠሩኝ ስትኾኑ ለእኔ ምን አለኝ? وَيَا قَوْمِ مَا لِي أَدْعُوكُمْ إِلَى النَّجَاةِ وَتَدْعُونَنِي إِلَى النَّارِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "መዳን" ለሚለው የገባው ቃል "ነጃህ" نَّجَاة እንደሆነ ልብ በል! ሰዎችን ወደ ኢሥላም ስንጠራ ከእሳት እንዲድኑ ነው። አምላካችን አሏህ ምሕረት አድርጎ ከአሳማሚ ቅጣት የሚያድነን ንስሓ ስንገባ፣ ስናምን፣ መልካም ሥራ ሥንሠራ እና ስንጸና ነው፦
20፥82 እኔም ለተጸጸተ፣ ላመነም፣ መልካምንም ለሠራ፣ ከዚያም ለተመራ ሰው በእርግጥ መሐሪ ነኝ። وَإِنِّي لَغَفَّارٌ لِّمَن تَابَ وَآمَنَ وَعَمِلَ صَالِحًا ثُمَّ اهْتَدَىٰ

"ለተጸጸተ" ሲል ንስሓን፣ "ላመነ" ሲል ኢማንን፣ "መልካምን ለሠራ" ሲል ዐሚሉ ሷሊሓትን፣ "ለተመራ" ሲል ኢሥቲቃማህን ያመለክታል፥ ኢሥቲቃማህ በተጸጸተበት ንስሓ፣ ባመነበት ኢማን እና በምንሠራው መልካም ሥራ መጽናት ነው። "ኢሥቲቃማህ" اِسْتِقَامَة የሚለው ቃል "ኢሥቲቃመ اِسْتَقَامَ ማለትም "ቆመ" ወይም "ጸና" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ጽናት" ማለት ነው፦
42፥15 ለዚህም ድንጋጌ ሰዎችን ጥራ፡፡ እንደታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ فَلِذَٰلِكَ فَادْعُ ۖ وَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ
11፥112 እንደ ታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ ከአንተ ጋር ያመኑትም ቀጥ ይበሉ፡፡ فَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ وَمَن تَابَ مَعَكَ

እነዚህ አንቀጽ ላይ "ቀጥ በል" ለሚለው የገባው ቃል "ኢሥተቂም" اسْتَقِمْ ሲሆን "ጽና" ማለት ነው፥ በቀጥተኛው መንገድ ላይ መጽናት ፍርሃት እና ሐዘን ሳይኖር የጀነት ለመሆን መበሰር ነው፦
46፥13 እነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ያሉ፣ ከዚያም ቀጥ ያሉ በእነርሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም። እነርሱም አያዝኑም፡፡ إِنَّ الَّذِينَ قَالُوا رَبُّنَا اللَّهُ ثُمَّ اسْتَقَامُوا فَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
41፥30 እነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ያሉ ከዚያም ቀጥ ያሉ «አትፍሩ፤ አትዘኑም፤ በዚያችም ተስፋ ቃል ትደረግላችሁ በነበራችሁት ገነት ተበሰሩ» በማለት በእነርሱ ላይ መላእክት ይወርዳሉ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ قَالُوا رَبُّنَا اللَّهُ ثُمَّ اسْتَقَامُوا تَتَنَزَّلُ عَلَيْهِمُ الْمَلَائِكَةُ أَلَّا تَخَافُوا وَلَا تَحْزَنُوا وَأَبْشِرُوا بِالْجَنَّةِ الَّتِي كُنتُمْ تُوعَدُون

እነዚህ አናቅጽ ላይ "ቀጥ ያሉ" ለሚለው ቃል የገባው "ኢሥተቃሙ" اسْتَقَامُوا ሲሆን አምላካችን አሏህ በዲኑል ኢሥላም ለሚጸኑ አማንያን ጀነትን ተስፋ ሰቷቸዋል፦
17፥108 ይላሉም «ጌታችን ጥራት ይገባው! እነሆ የጌታችን ተስፋ ተፈጻሚ ነው፡፡» وَيَقُولُونَ سُبْحَانَ رَبِّنَا إِن كَانَ وَعْدُ رَبِّنَا لَمَفْعُولًا
19፥61 የመኖሪያን ገነቶች ያችን አልረሕማን ለባሮቹ በሩቅ ኾነው ሳሉ ተስፋ ቃል የገባላቸውን ይገባሉ፡፡ እርሱ ተስፋው ተፈጻሚ ነውና። جَنَّاتِ عَدْنٍ الَّتِي وَعَدَ الرَّحْمَـٰنُ عِبَادَهُ بِالْغَيْبِ ۚ إِنَّهُ كَانَ وَعْدُهُ مَأْتِيًّا

ለጽናት ጉልኅ ሚናህ ያለው አሏህን ለመገናኘት ተስፋ ማድረግ ነው፥ ከእዝነቱ ተስፋ መቁረጥ ግን ለጽናት እንቅፋት ነው፦
29፥5 የአላህን መገናኘት ተስፋ የሚያደርግ ሰው ይዘጋጅ፡፡ የአላህ ቀጠሮ በእርግጥ መጪ ነውና፡፡ እርሱም ሰሚው ዐዋቂው ነው፡፡ مَن كَانَ يَرْجُو لِقَاءَ اللَّهِ فَإِنَّ أَجَلَ اللَّهِ لَآتٍ ۚ وَهُوَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ
29፥23 እነዚያም በአላህ አንቀጾችና በመገናኘቱ የካዱ እነዚያ ከእዝነቴ ተስፋን ቆረጡ፡፡ እነዚያም ለእነሱ አሳማሚ ቅጣት አላቸው፡፡ وَالَّذِينَ كَفَرُوا بِآيَاتِ اللَّهِ وَلِقَائِهِ أُولَـٰئِكَ يَئِسُوا مِن رَّحْمَتِي وَأُولَـٰئِكَ لَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ

አምላካችን አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነውና በሰጠን ተስፋ ወደ እርሱ ቀጥ ማለት ለጀነት ይዳርጋል፦
31፥6 እንዲህ በላቸው «እኔ መሰላችሁ ሰው ብቻ ነኝ፡፡ አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው ወደ እርሱም "ቀጥ በሉ" ምሕረትንም ለምኑት» ማለት ወደ እኔ ይወረድልኛል፡፡ ለአጋሪዎቹም ወዮላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا أَنَا بَشَرٌ مِّثْلُكُمْ يُوحَىٰ إِلَيَّ أَنَّمَا إِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ فَاسْتَقِيمُوا إِلَيْهِ وَاسْتَغْفِرُوهُ ۗ وَوَيْلٌ لِّلْمُشْرِكِينَ

አሏህ በዲኑል ኢሥላም ያጽናን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://hottg.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም


>>Click here to continue<<

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)