TG Telegram Group & Channel
ወሒድ የንጽጽር ማኅደር | United States America (US)
Create: Update:

አሚር

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

9፥71 ምእመናን እና ምእምናት ከፊሎቻቸው ለከፊሉ ረዳቶች ናቸው፡፡ በደግ ነገር ያዛሉ፤ ከክፉም ይከለክላሉ፡፡ وَالْمُؤْمِنُونَ وَالْمُؤْمِنَاتُ بَعْضُهُمْ أَوْلِيَاءُ بَعْضٍ ۚ يَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَيَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ

"አምር" أَمْر የሚለው ቃል "አመረ" أَمَرَ ማለትም "አዘዘ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ትእዛዝ" ማለት ነው፥ በመልካም የሚያዙ አዛዥ "አሚር" أَمِير ሲባሉ የሚታዘዙ ታዛዥ ደግሞ "መእሙር" مَأْمُور ይባላሉ፦
3፥104 ከእናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ በመልካም ሥራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ፡፡ እነዚያም እነርሱ የሚድኑ ናቸው፡፡ وَلْتَكُن مِّنكُمْ أُمَّةٌ يَدْعُونَ إِلَى الْخَيْرِ وَيَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَيَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ ۚ وَأُولَـٰئِكَ هُمُ الْمُفْلِحُونَ
9፥71 ምእመናን እና ምእምናት ከፊሎቻቸው ለከፊሉ ረዳቶች ናቸው፡፡ በደግ ነገር ያዛሉ፤ ከክፉም ይከለክላሉ፡፡ وَالْمُؤْمِنُونَ وَالْمُؤْمِنَاتُ بَعْضُهُمْ أَوْلِيَاءُ بَعْضٍ ۚ يَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَيَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ

በደግ ነገር በማዘዝ እና በክፉ ነገር በመከልከል የምታዝ ሴት አማኝ "አሚራህ" أَمِيرَة ትባላለች፥ አሏህ በከለከለው መጥፎ ነገር የሚከለክል እና ባዘዘው መልካም ነገር የሚያዝ አሚርን መታዘዝ ግዴታ ነው፦
4፥59 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ተገዙ! መልእክተኛውን እና ከእናንተ የትእዛዝ ባለቤቶችን ታዘዙ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَطِيعُوا اللَّهَ وَأَطِيعُوا الرَّسُولَ وَأُولِي الْأَمْرِ مِنكُمْ ۖ

"ከ" የሚለው መስተዋድድ ያለበት "እናንተ" የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው ምእመናንን ብቻ ሲሆን "ኡውሊል አምር" أُولِي الْأَمْر የተባሉት አሚራት ከምእመናን ብቻ መሆናቸውን ቁልጭ አርጎ ያሳያል። አሚራትን መታዘዝ በእርግጥ ነቢያችንን"ﷺ" መታዘዝ ነው፥ አሚራትን ማመጽ ነቢያችንን"ﷺ" ማመጽ ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 33, ሐዲስ 46
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "እኔን የሚታዘዝ በእርግጥ አሏህን ታዘዘ፥ እኔን የሚያምጽ በእርግጥ አሏህን አመጸ። አሚር የሚታዘዝ በእርግጥ እኔን ታዘዘ፥ አሚርን የሚያምጽ በእርግጥ እኔን አመጸ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ مَنْ أَطَاعَنِي فَقَدْ أَطَاعَ اللَّهَ وَمَنْ يَعْصِنِي فَقَدْ عَصَى اللَّهَ وَمَنْ يُطِعِ الأَمِيرَ فَقَدْ أَطَاعَنِي وَمَنْ يَعْصِ الأَمِيرَ فَقَدْ عَصَانِي ‏"‏

አምላካችን አሏህ አሚራትን የምንታዘዝ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://hottg.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

አሚር

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

9፥71 ምእመናን እና ምእምናት ከፊሎቻቸው ለከፊሉ ረዳቶች ናቸው፡፡ በደግ ነገር ያዛሉ፤ ከክፉም ይከለክላሉ፡፡ وَالْمُؤْمِنُونَ وَالْمُؤْمِنَاتُ بَعْضُهُمْ أَوْلِيَاءُ بَعْضٍ ۚ يَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَيَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ

"አምር" أَمْر የሚለው ቃል "አመረ" أَمَرَ ማለትም "አዘዘ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ትእዛዝ" ማለት ነው፥ በመልካም የሚያዙ አዛዥ "አሚር" أَمِير ሲባሉ የሚታዘዙ ታዛዥ ደግሞ "መእሙር" مَأْمُور ይባላሉ፦
3፥104 ከእናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ በመልካም ሥራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ፡፡ እነዚያም እነርሱ የሚድኑ ናቸው፡፡ وَلْتَكُن مِّنكُمْ أُمَّةٌ يَدْعُونَ إِلَى الْخَيْرِ وَيَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَيَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ ۚ وَأُولَـٰئِكَ هُمُ الْمُفْلِحُونَ
9፥71 ምእመናን እና ምእምናት ከፊሎቻቸው ለከፊሉ ረዳቶች ናቸው፡፡ በደግ ነገር ያዛሉ፤ ከክፉም ይከለክላሉ፡፡ وَالْمُؤْمِنُونَ وَالْمُؤْمِنَاتُ بَعْضُهُمْ أَوْلِيَاءُ بَعْضٍ ۚ يَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَيَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ

በደግ ነገር በማዘዝ እና በክፉ ነገር በመከልከል የምታዝ ሴት አማኝ "አሚራህ" أَمِيرَة ትባላለች፥ አሏህ በከለከለው መጥፎ ነገር የሚከለክል እና ባዘዘው መልካም ነገር የሚያዝ አሚርን መታዘዝ ግዴታ ነው፦
4፥59 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ተገዙ! መልእክተኛውን እና ከእናንተ የትእዛዝ ባለቤቶችን ታዘዙ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَطِيعُوا اللَّهَ وَأَطِيعُوا الرَّسُولَ وَأُولِي الْأَمْرِ مِنكُمْ ۖ

"ከ" የሚለው መስተዋድድ ያለበት "እናንተ" የሚለው ተውላጠ ስም የሚያመለክተው ምእመናንን ብቻ ሲሆን "ኡውሊል አምር" أُولِي الْأَمْر የተባሉት አሚራት ከምእመናን ብቻ መሆናቸውን ቁልጭ አርጎ ያሳያል። አሚራትን መታዘዝ በእርግጥ ነቢያችንን"ﷺ" መታዘዝ ነው፥ አሚራትን ማመጽ ነቢያችንን"ﷺ" ማመጽ ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 33, ሐዲስ 46
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "እኔን የሚታዘዝ በእርግጥ አሏህን ታዘዘ፥ እኔን የሚያምጽ በእርግጥ አሏህን አመጸ። አሚር የሚታዘዝ በእርግጥ እኔን ታዘዘ፥ አሚርን የሚያምጽ በእርግጥ እኔን አመጸ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ مَنْ أَطَاعَنِي فَقَدْ أَطَاعَ اللَّهَ وَمَنْ يَعْصِنِي فَقَدْ عَصَى اللَّهَ وَمَنْ يُطِعِ الأَمِيرَ فَقَدْ أَطَاعَنِي وَمَنْ يَعْصِ الأَمِيرَ فَقَدْ عَصَانِي ‏"‏

አምላካችን አሏህ አሚራትን የምንታዘዝ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://hottg.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም


>>Click here to continue<<

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)