TG Telegram Group & Channel
ርጢን ሚዲያ ( Ritin Media ) | United States America (US)
Create: Update:

✥✥✥ሦስት ሌሊት እና መዓልት✥✥✥

👉 ጥያቄ:- ጌታችን ሦስት ቀንና ሌሊት በከርሠ መቃብር (በመቃብር ሆድ/ውስጥ/) ቆየ ስንል ኣቆጣጠሩ እንዴት ነው?

👉 መልስ:- በመጀመሪያ የጌታችን የመቃብር ውስጥ ቆይታ ሦስት ቀንና ሌሊት መሆኑን የገለጠልን ራሱ መድኅነ ዓለም ክርስትስ ነው ይኸውም :- " ዮናስ በዓሣ አንባሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ ÷ እንዲሁም የሰው "ልጅ (ክርስቶስ) በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል። " (የማቴ ወን12÷40) በተጨማሪም " ጌታ ኢየሱስም መልሶ:-- ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስት ዕለትም አነሣዋለሁ አላቸው " (የዮሓ ወን 2÷19) " ስለዚህ የጌታችን የመቃብር ውስጥ ቆይታ ሦስት ቀንና ሌሊት መሆኑን እርግጥ ነው።

➛ አቆጣጠሩ

፩— ጌታችን በዕለተ አርብ በእኩለ ቀን ስድስት ሰዓት ተሰቅሎ በዘጠኝ ሰዓት በራሱ ሥልጣን ነፍሱን ከሥጋው ለየ በአስራ አንድ ሰዓትም ወደ መቃብር ወረደ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ስንቆጥር አርብ ከ11—12 ሰዓት ያለው አንዱ ሰዓት እንደ አንድ ዕለት(ቀንና ሌሊት) እንቆጥረዋለን።

➛ (ማስታወሻ:– ዕለት ማለት በ24 ሰዓት ውስጥ ያለውን ቀንና ሌሊትን የሚገልጥ ሲሆን ቀን የምንለው ደግሞ 12 ሰዓት ብርሃንን ሲወክል ሌሊት ደግሞ የጨለማውን 12 ሰዓት ይወክላል። ከዚህ ላይ ልናስተው የሚገባው ለዕለት (ለ24 ሰዓት) ቀኑ ሳይሆን ሌሊቱ ነው የሚቀድመው ይህን የሚያስረዳ፦

➛ ከኦሪ ዘፍ 1÷5 ጀምሮ በተከታታይ " ማታም ሆነ÷ ጠዋትም ሆነ " በማለት ለዕለት ጨለማው እንጂ ቀኑ እንደማይቀድም ገልጦልናል

- ለምሳሌ በተለምዶ የሐሙስ ሌሊት የምንለው የአርብ እንጂ የሐሙስ አይደለም ስለዚህ በዚህ ትክክለኛ የመጽሓፍ ቅዱስ አቆጣጠርን መሠረት አድርገን ጌታችን አርብን ከቀኑ11 ወደ መቃብር ወረደ ስንል ዕለተ አርብ ልታልቅ የቀረው አንድ ሰዓት ብቻ ቢሆንም ይህች ከ11–12 ያለችው አንድ ሰዓት የዕለተ አርብን 24 ሰዓት ሁሉ ትወክላለች ለምሳሌ በዚህች ሰዓት ላይ ያለ ሰው ዛሬ አርብ ነው ይላል እንጂ አንድ ሰዓት ስለቀራት ዛሬ ቅዳሜ ነው አይልም ስለዚህ አርብ ከ11–12 ያለችው አንድ ሰዓት ዕለቱን (24 ሰዓቱን) ወክላ ጌታችን በመቃብር ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ቆየ የተባለበትን አንዱን ቀንና ሌሊት ታስቆጥረናለች።

— በመቀጠልም በተለምዶ አርብ ሌሊት ከሚባለው ከቅዳሜ12 ሰዓት ጀምሮ የምናድርበት 12 ሰዓት እና ነግቶም የምንውልበት 12 ሰዓት (በድምሩ 24 ሰዓት ሌሊት እና ቀን) ሁለተኛ የመቃብር ውስጥ ቆይታ ይሆናል።

— በተለምዶ ቅዳሜ ሌሊት ከሚባለው ከእሁድ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ጌታችን እስተነሳበት እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ያሉት ስድስት ሰዓታት የዕለተ እሁድን 24 ሰዓት ወክለው ሦስተኛውን የመቃብር ውስጥ ቆይታ ያስቆጥሩናል። ስለዚህ:–

+ አርብ ከ11—12 (ያለው አንድ ሰዓት አንድ ሌሊትና ቀን)
+ ቅዳሜ ከ12—12(ሌሊት)፣ ከ12—12 (ቀን) ሁለተኛ ሌሊትና ቀን
+ እሁድ ከ12—6 ያለው ስድስት ሰዓት ሦስተኛ ሌሊትና ቀን ይሆናል። ይህ የመጀመሪያው አቆጣጠር ነው።

፪— ጌታችን አርብ ጠዋት ሦስት ሰዓት ይሰቀል ይሙት ተብሎ ተፈርዶበታልና ሊቃውንትም ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ያለውን እንደሞት እንደመቃብር ቆይታ በመቁጠር በወንጌል እንደተገለጠልን (የማር ወን 16÷24 ጀምሮ ይመልከቱ) ከ3—6 ሰዓት ብርሃን ነበር ከ6—9 ደግሞ ጨለማ ሆኗል ይህም ብርሃን እና ጨለማ እንደ አንድ ዕለት ይቆጠራል።

— በዚያሁ በዕለተ አርብ ጌታችን ነፍሱን ከሥጋው በሥልጣኑ ከለየበት ከዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ እስከ አስራ ሁለት ሰዓት ብርሃን ሆኗል÷ በተለምዶ አርብ ሌሊት ከሚባለው ከቅዳሜ አስራ ሁለት ሰዓት እስከ ጠዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ጨለማ ሆኗል ይህም ብርሃን እና ጨለማ ሁለተኛ ዕለት ይሆናል።

— ቅዳሜ ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ያለው ብርሃን እና በተለምዶ ቅዳሜ ሌሊት ከሚባለው ከእሁድ 12 ሰዓት ጌታችን በሥልጣኑ እስከተነሣበት እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ያለው ጨለማ  

✥✥✥ሦስት ሌሊት እና መዓልት✥✥✥

👉 ጥያቄ:- ጌታችን ሦስት ቀንና ሌሊት በከርሠ መቃብር (በመቃብር ሆድ/ውስጥ/) ቆየ ስንል ኣቆጣጠሩ እንዴት ነው?

👉 መልስ:- በመጀመሪያ የጌታችን የመቃብር ውስጥ ቆይታ ሦስት ቀንና ሌሊት መሆኑን የገለጠልን ራሱ መድኅነ ዓለም ክርስትስ ነው ይኸውም :- " ዮናስ በዓሣ አንባሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ ÷ እንዲሁም የሰው "ልጅ (ክርስቶስ) በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል። " (የማቴ ወን12÷40) በተጨማሪም " ጌታ ኢየሱስም መልሶ:-- ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስት ዕለትም አነሣዋለሁ አላቸው " (የዮሓ ወን 2÷19) " ስለዚህ የጌታችን የመቃብር ውስጥ ቆይታ ሦስት ቀንና ሌሊት መሆኑን እርግጥ ነው።

➛ አቆጣጠሩ

፩— ጌታችን በዕለተ አርብ በእኩለ ቀን ስድስት ሰዓት ተሰቅሎ በዘጠኝ ሰዓት በራሱ ሥልጣን ነፍሱን ከሥጋው ለየ በአስራ አንድ ሰዓትም ወደ መቃብር ወረደ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ስንቆጥር አርብ ከ11—12 ሰዓት ያለው አንዱ ሰዓት እንደ አንድ ዕለት(ቀንና ሌሊት) እንቆጥረዋለን።

➛ (ማስታወሻ:– ዕለት ማለት በ24 ሰዓት ውስጥ ያለውን ቀንና ሌሊትን የሚገልጥ ሲሆን ቀን የምንለው ደግሞ 12 ሰዓት ብርሃንን ሲወክል ሌሊት ደግሞ የጨለማውን 12 ሰዓት ይወክላል። ከዚህ ላይ ልናስተው የሚገባው ለዕለት (ለ24 ሰዓት) ቀኑ ሳይሆን ሌሊቱ ነው የሚቀድመው ይህን የሚያስረዳ፦

➛ ከኦሪ ዘፍ 1÷5 ጀምሮ በተከታታይ " ማታም ሆነ÷ ጠዋትም ሆነ " በማለት ለዕለት ጨለማው እንጂ ቀኑ እንደማይቀድም ገልጦልናል

- ለምሳሌ በተለምዶ የሐሙስ ሌሊት የምንለው የአርብ እንጂ የሐሙስ አይደለም ስለዚህ በዚህ ትክክለኛ የመጽሓፍ ቅዱስ አቆጣጠርን መሠረት አድርገን ጌታችን አርብን ከቀኑ11 ወደ መቃብር ወረደ ስንል ዕለተ አርብ ልታልቅ የቀረው አንድ ሰዓት ብቻ ቢሆንም ይህች ከ11–12 ያለችው አንድ ሰዓት የዕለተ አርብን 24 ሰዓት ሁሉ ትወክላለች ለምሳሌ በዚህች ሰዓት ላይ ያለ ሰው ዛሬ አርብ ነው ይላል እንጂ አንድ ሰዓት ስለቀራት ዛሬ ቅዳሜ ነው አይልም ስለዚህ አርብ ከ11–12 ያለችው አንድ ሰዓት ዕለቱን (24 ሰዓቱን) ወክላ ጌታችን በመቃብር ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ቆየ የተባለበትን አንዱን ቀንና ሌሊት ታስቆጥረናለች።

— በመቀጠልም በተለምዶ አርብ ሌሊት ከሚባለው ከቅዳሜ12 ሰዓት ጀምሮ የምናድርበት 12 ሰዓት እና ነግቶም የምንውልበት 12 ሰዓት (በድምሩ 24 ሰዓት ሌሊት እና ቀን) ሁለተኛ የመቃብር ውስጥ ቆይታ ይሆናል።

— በተለምዶ ቅዳሜ ሌሊት ከሚባለው ከእሁድ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ጌታችን እስተነሳበት እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ያሉት ስድስት ሰዓታት የዕለተ እሁድን 24 ሰዓት ወክለው ሦስተኛውን የመቃብር ውስጥ ቆይታ ያስቆጥሩናል። ስለዚህ:–

+ አርብ ከ11—12 (ያለው አንድ ሰዓት አንድ ሌሊትና ቀን)
+ ቅዳሜ ከ12—12(ሌሊት)፣ ከ12—12 (ቀን) ሁለተኛ ሌሊትና ቀን
+ እሁድ ከ12—6 ያለው ስድስት ሰዓት ሦስተኛ ሌሊትና ቀን ይሆናል። ይህ የመጀመሪያው አቆጣጠር ነው።

፪— ጌታችን አርብ ጠዋት ሦስት ሰዓት ይሰቀል ይሙት ተብሎ ተፈርዶበታልና ሊቃውንትም ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ያለውን እንደሞት እንደመቃብር ቆይታ በመቁጠር በወንጌል እንደተገለጠልን (የማር ወን 16÷24 ጀምሮ ይመልከቱ) ከ3—6 ሰዓት ብርሃን ነበር ከ6—9 ደግሞ ጨለማ ሆኗል ይህም ብርሃን እና ጨለማ እንደ አንድ ዕለት ይቆጠራል።

— በዚያሁ በዕለተ አርብ ጌታችን ነፍሱን ከሥጋው በሥልጣኑ ከለየበት ከዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ እስከ አስራ ሁለት ሰዓት ብርሃን ሆኗል÷ በተለምዶ አርብ ሌሊት ከሚባለው ከቅዳሜ አስራ ሁለት ሰዓት እስከ ጠዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ጨለማ ሆኗል ይህም ብርሃን እና ጨለማ ሁለተኛ ዕለት ይሆናል።

— ቅዳሜ ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ያለው ብርሃን እና በተለምዶ ቅዳሜ ሌሊት ከሚባለው ከእሁድ 12 ሰዓት ጌታችን በሥልጣኑ እስከተነሣበት እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ያለው ጨለማ  


>>Click here to continue<<

ርጢን ሚዲያ ( Ritin Media )




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)