TG Telegram Group & Channel
Nolawi ኖላዊ | United States America (US)
Create: Update:

የሕይወት ሥነ ሥርዓት 10

…. አለባበስህን ጠብቅ (ካለፈው የቀጠለ)

አንዳንድ ሰዎች ስለ ራሳቸው በአፋቸው ብዙ ያወራሉ ፤ ሌሎች ደግሞ በልብሳቸው ስለራሳቸው ብዙ ያወራሉ ። ልብስ ዕርቃን መሸፈኛ ነው ። ዕራቁታችንን የሚያውቀንና የሚቀበለን እግዚአብሔር ብቻ ነው ። ሰው ያለ መሸፈኛ የማይቆም ፍጡር ነው። በሰው ፊት ለመቆም ልብስ ፣ በእግዚአብሔር ፊት ለመቆም ጸጋ ያስፈልገዋል ። ልብስ ከመሠረታዊ ፍላጎቶች አንዱ ነው ። ልብስ ሰዎች ጤናቸውን የሚጠብቁበትም ነው ። የአእምሮ በሥራ ላይ መሆን አንዱ ምልክት ልብስ መልበስ ነው ። በርግጥ እንደ ምዕራባውያን መራቆትም ፣ እንደ ዐረብ ሴቶች መጨቆንም ሁለቱም ሚዛናዊ መሆን አለበት ። ልብስ ሀብትን ማሳያ ፣ ቁንጅናን ማጉያ አድርገው የሚጠቀሙበት አሉ ። የሰው ልጅ ለራሱና ለሰዎች ብሎ የሚያደርገው ነገር ካለ እርሱ ልብስ ይበላል። ልብስ ሙሉ ሰውን ፣ ሹምን ፣ ካህንን ለመለየት የሚውል ነው ። ልብስ ትልቅ የክብር መግለጫ ነው ። የሰው ልጆችም እንደ ዕፀ በለስ በልብስ የሚፈተኑ ሆነዋል ። ላለበሰና ለለበሰ ሰው እኩል ክብር የላቸውም ። ኖር ለልብሱ ይባላል ። ኖር ለእርሱ ሳይሆን ኖር ለልብሱ መባሉ ተገቢ አይደለም።

የዓለማችን ትልቁ ምርት ከምግብ ቀጥሎ ልብስ ነው ፤ ከዚያ ቀጥሎ መድኃኒት ሊሆን ይችላል ። ጸሎታችንም “የዕለት ጉርሴን ፣ የዓመት ልብሴን አትንሣኝ” የሚል ነው ። ልብስ የሚያገለግለው ዕራቁትን ለመሸፈን ብቻ ስይሆን የሰውነት ቅርጽንም ለመሸፈን ነው ። የሰውነትን ቅርጽን ማሳየት በራሱ እንደ መራቆት ነው ። ልብስ የሰው ልጆችን ውበት የሚያላብሳቸው ነው ። ዕራቁቱን የሚያምር ከሕፃን በቀር ማግኘት አስቸጋሪ ነው ። ልብስ ከቅድስና መለኪያዎች አንዱ ነው ። ብዙ ጊዜ ልቅ አለባበስን በሚመለከት ከወንዶች ይልቅ ሴቶች ይፈተናሉ ። “የሴት ክብር ባሏ ሲገልጣት እንጂ በአደባባይ ተገልጣ ስትለምን አይደለም” ይባላል ። ሰዎች ሁሉ በዓለም ላይ ያሉ ወገኖች ልብስን በተለያየ ዓላማ ሊለብሱ ይችላሉ ።

የመጀመሪያው ፋሽን ለመከተል ነው ። የፋሽኑ ዓለም እንቅልፍ የለውም ። የሰዎችን ቀልብ ለመሳብና ገንዘብ ለመልቀም ሌሊትና ቀን ይተጋል ። የፋሽኑ ዓለም ከአጋንንት ጋር የእውቀት ልውውጥ እንደሚያደርግ ብዙ ሲነገር ኖሯል ። ሰዎችን ምን ይማርካቸዋል ? በማለት ያጠናሉ ፣ ያስጠናሉ ። በይበልጥ ዝሙትን የሚያስፋፋ ፣ ሥጋዊ ስሜትን አድራሻ ያደረገ ንድፍ ይሠራል ። ሰይጣን አያመነዝርም ፣ ግን ዝሙትን ይወዳል ። ክፉ ነገሥታትም ትውልድ የዝሙት እስረኛ ከሆነ እነርሱን ስለማያያቸው በዚህ ጦር ወግተው ያቆስሉታል ። ፋሽኑ ከተሰፋ ልብስ እስከ ተቀደደ ልብስ ፣ ከፍዝ እስከ ቦጌ ቀለም እየለዋወጠ ያመጣል ። የሰውን ወረተኛነት ትልቅ የገቢ ምንጭ በማድረግ ጠባዩን ይዋጉታል ። ዓለምን የሚመሩ ጥቂት ሰዎች ናቸው ። ዕውቅ ሰዎች ያንን ልብስ ለብሰው ሲታዩ ጎጋው ሕዝብ ይከተላል ። የልብሱ ትርጉም ምን መሆኑን እንኳ ሳይጠይቅ የለበሰውን እየጣለ ያንን ይሸምታል ። የፋሽኑ ዓለም የጊዜ ክፍተት እየሰጠ የሄደውን ፋሽን መልሶ እያመጣ አዲሱን ትውልድ ይጫወትበታል ። ፋሽን ተከታይ የሆኑ ዘመናዊና ንቁ ሰዎች እንደሆኑ ይገምታሉ ፣ ሰዎችም እንደ ዘመናዊ ያስቧቸዋል። ለልብሱ የሚጨነቅ ለነፍሱ የማይጨነቅ ደንቆሮ ነው ። እውነተኛ ሥልጣኔ ግን ከልብስ ያለፈ ነው ።

ሁለተኛው ማራኪ ለመሆን ነው ። ሴቶች ወንዶችን ለመሳብ ፣ ወንዶች ሴቶችን ለመሳብ ይለብሳሉ። በእጃቸው ላይ የሚቀቡት ሽቶ ሳይቀር የሚጨብጡት ሰው እጅ ላይ ታትሞ እንዲቀር ፣ አካባቢው ሁሉ በእነርሱ ጠረን እንዲታወድ ይፈልጋሉ ፤ ይህ መለስተኛ ጣዖትነት ነው ። ለዚህ ነው “ሽቶ የዝሙት ቅብዐ መንግሥት ነው” የሚባለው ። ከወደድነው ሁሉ ጋር አንኖርም ፣ የወደደን ሁሉም ከእኛ ጋር አይኖርም ። ከልብሳችን ይልቅ ጠባያችን ሳቢ ቢሆን የሰው ዋጋ እናገኛለን ። አሊያ የሸቀጥ ማስታወቂያ ሆነን እንቀራለን ። በዕድሜአቸው ዘመን ምንም የሚነገር ታሪክ የሌላቸው ፣ ልብስ ሲገዙ ፣ ሽቶ ሲያጠራቅሙ ኖረው ሞቱ የሚባሉ ብዙ ምስኪን ሰዎች አሉ።

ይቀጥላል

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 1 ቀን 2016 ዓ.ም.

የሕይወት ሥነ ሥርዓት 10

…. አለባበስህን ጠብቅ (ካለፈው የቀጠለ)

አንዳንድ ሰዎች ስለ ራሳቸው በአፋቸው ብዙ ያወራሉ ፤ ሌሎች ደግሞ በልብሳቸው ስለራሳቸው ብዙ ያወራሉ ። ልብስ ዕርቃን መሸፈኛ ነው ። ዕራቁታችንን የሚያውቀንና የሚቀበለን እግዚአብሔር ብቻ ነው ። ሰው ያለ መሸፈኛ የማይቆም ፍጡር ነው። በሰው ፊት ለመቆም ልብስ ፣ በእግዚአብሔር ፊት ለመቆም ጸጋ ያስፈልገዋል ። ልብስ ከመሠረታዊ ፍላጎቶች አንዱ ነው ። ልብስ ሰዎች ጤናቸውን የሚጠብቁበትም ነው ። የአእምሮ በሥራ ላይ መሆን አንዱ ምልክት ልብስ መልበስ ነው ። በርግጥ እንደ ምዕራባውያን መራቆትም ፣ እንደ ዐረብ ሴቶች መጨቆንም ሁለቱም ሚዛናዊ መሆን አለበት ። ልብስ ሀብትን ማሳያ ፣ ቁንጅናን ማጉያ አድርገው የሚጠቀሙበት አሉ ። የሰው ልጅ ለራሱና ለሰዎች ብሎ የሚያደርገው ነገር ካለ እርሱ ልብስ ይበላል። ልብስ ሙሉ ሰውን ፣ ሹምን ፣ ካህንን ለመለየት የሚውል ነው ። ልብስ ትልቅ የክብር መግለጫ ነው ። የሰው ልጆችም እንደ ዕፀ በለስ በልብስ የሚፈተኑ ሆነዋል ። ላለበሰና ለለበሰ ሰው እኩል ክብር የላቸውም ። ኖር ለልብሱ ይባላል ። ኖር ለእርሱ ሳይሆን ኖር ለልብሱ መባሉ ተገቢ አይደለም።

የዓለማችን ትልቁ ምርት ከምግብ ቀጥሎ ልብስ ነው ፤ ከዚያ ቀጥሎ መድኃኒት ሊሆን ይችላል ። ጸሎታችንም “የዕለት ጉርሴን ፣ የዓመት ልብሴን አትንሣኝ” የሚል ነው ። ልብስ የሚያገለግለው ዕራቁትን ለመሸፈን ብቻ ስይሆን የሰውነት ቅርጽንም ለመሸፈን ነው ። የሰውነትን ቅርጽን ማሳየት በራሱ እንደ መራቆት ነው ። ልብስ የሰው ልጆችን ውበት የሚያላብሳቸው ነው ። ዕራቁቱን የሚያምር ከሕፃን በቀር ማግኘት አስቸጋሪ ነው ። ልብስ ከቅድስና መለኪያዎች አንዱ ነው ። ብዙ ጊዜ ልቅ አለባበስን በሚመለከት ከወንዶች ይልቅ ሴቶች ይፈተናሉ ። “የሴት ክብር ባሏ ሲገልጣት እንጂ በአደባባይ ተገልጣ ስትለምን አይደለም” ይባላል ። ሰዎች ሁሉ በዓለም ላይ ያሉ ወገኖች ልብስን በተለያየ ዓላማ ሊለብሱ ይችላሉ ።

የመጀመሪያው ፋሽን ለመከተል ነው ። የፋሽኑ ዓለም እንቅልፍ የለውም ። የሰዎችን ቀልብ ለመሳብና ገንዘብ ለመልቀም ሌሊትና ቀን ይተጋል ። የፋሽኑ ዓለም ከአጋንንት ጋር የእውቀት ልውውጥ እንደሚያደርግ ብዙ ሲነገር ኖሯል ። ሰዎችን ምን ይማርካቸዋል ? በማለት ያጠናሉ ፣ ያስጠናሉ ። በይበልጥ ዝሙትን የሚያስፋፋ ፣ ሥጋዊ ስሜትን አድራሻ ያደረገ ንድፍ ይሠራል ። ሰይጣን አያመነዝርም ፣ ግን ዝሙትን ይወዳል ። ክፉ ነገሥታትም ትውልድ የዝሙት እስረኛ ከሆነ እነርሱን ስለማያያቸው በዚህ ጦር ወግተው ያቆስሉታል ። ፋሽኑ ከተሰፋ ልብስ እስከ ተቀደደ ልብስ ፣ ከፍዝ እስከ ቦጌ ቀለም እየለዋወጠ ያመጣል ። የሰውን ወረተኛነት ትልቅ የገቢ ምንጭ በማድረግ ጠባዩን ይዋጉታል ። ዓለምን የሚመሩ ጥቂት ሰዎች ናቸው ። ዕውቅ ሰዎች ያንን ልብስ ለብሰው ሲታዩ ጎጋው ሕዝብ ይከተላል ። የልብሱ ትርጉም ምን መሆኑን እንኳ ሳይጠይቅ የለበሰውን እየጣለ ያንን ይሸምታል ። የፋሽኑ ዓለም የጊዜ ክፍተት እየሰጠ የሄደውን ፋሽን መልሶ እያመጣ አዲሱን ትውልድ ይጫወትበታል ። ፋሽን ተከታይ የሆኑ ዘመናዊና ንቁ ሰዎች እንደሆኑ ይገምታሉ ፣ ሰዎችም እንደ ዘመናዊ ያስቧቸዋል። ለልብሱ የሚጨነቅ ለነፍሱ የማይጨነቅ ደንቆሮ ነው ። እውነተኛ ሥልጣኔ ግን ከልብስ ያለፈ ነው ።

ሁለተኛው ማራኪ ለመሆን ነው ። ሴቶች ወንዶችን ለመሳብ ፣ ወንዶች ሴቶችን ለመሳብ ይለብሳሉ። በእጃቸው ላይ የሚቀቡት ሽቶ ሳይቀር የሚጨብጡት ሰው እጅ ላይ ታትሞ እንዲቀር ፣ አካባቢው ሁሉ በእነርሱ ጠረን እንዲታወድ ይፈልጋሉ ፤ ይህ መለስተኛ ጣዖትነት ነው ። ለዚህ ነው “ሽቶ የዝሙት ቅብዐ መንግሥት ነው” የሚባለው ። ከወደድነው ሁሉ ጋር አንኖርም ፣ የወደደን ሁሉም ከእኛ ጋር አይኖርም ። ከልብሳችን ይልቅ ጠባያችን ሳቢ ቢሆን የሰው ዋጋ እናገኛለን ። አሊያ የሸቀጥ ማስታወቂያ ሆነን እንቀራለን ። በዕድሜአቸው ዘመን ምንም የሚነገር ታሪክ የሌላቸው ፣ ልብስ ሲገዙ ፣ ሽቶ ሲያጠራቅሙ ኖረው ሞቱ የሚባሉ ብዙ ምስኪን ሰዎች አሉ።

ይቀጥላል

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 1 ቀን 2016 ዓ.ም.


>>Click here to continue<<

Nolawi ኖላዊ




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)