በዱዓችሁ
***
መካከለኛውን ምሥራቅ አዲስ ገፅታ እናላብሳለን ብለው የተነሱ ሰዎች እየተረዳዱ ይቃወሙናል ብለው ያሰቡትን ይደቁሱ ይዘዋል። በቀናት ሂደት የአዝራኢል አቅም መዳከም የታያት አሜሪካ እሷ የጀመረችውን ተቀብላ ጨርሳላታለች። በኢራን ላይ የተደረገውን ጥቃት ምዕራባውያን ሲደግፉ ሙስሊሞች እና ዐረቦች ኮንነዋል ። ያልኮነኑት ቢያንስ ጉዳዩ አሳስቦናል ብለዋል።
በኢራን ጉዳይ በተሸፈነችውና በተረሣችው ገዛ ባለፉት አሥር ቀናት ውስጥ ብቻ በአማካይ በቀን ከ100 ሰው በላይ ሲገደል ነው የሰነበተው ። በዚህም የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 56 ሺህ ደርሷል። ገዛውያን ጥሙ ረሀቡና ቦንቡ አሳር ሆኖባቸዋል። የጦርነቱና የከበባው ጉዳዩ በቅርብ ማብቂያ ያለው አይመስልም ።
ሙስሊሙ መንግሥታት ኅይል ቢኖራቸው እንኳ አንድነት የላቸውም ። ሁሉም በየራሣቸው ጉዳይ ተወጥረዋል። አንዳንድ ጊዜ ይህን ልብ ሰባሪ ግፍ ዝምብለው ከሚመለከቱ ምናለ በልመናና በተማጽኖ እንኳ ማስቆም በቻሉ ያሠኘኛል።
ቲስበሑ
https://hottg.com/MuhammedSeidAbx
>>Click here to continue<<
