ውሸት አስነዋሪ ባህሪ ነው ። ውሸት የሙናፊቆች መለያ ነው ። ውሸት ማንነትን ከሚያረክሱ መገለጫዎች ውስጥ አንዱ ነው ። ታላቁ ነብይ ውሸት ወደ ወንጀሎች እንደሚመራ ገልፀዋል ። ውሸትን የሚዳፈር ሰው ሌሎች ትልልቅ ወንጀሎች ውስጥም ሊነከር የቀረበ ነው ። ውሸትን የሚያበዛ ሰው አላህ ዘንድ “ ውሸታም” ተብሎ ይፃፋል !!!
ባጠቃላይ ውሸት የሰዎችን ታማኝነት የሚሰባብር ቆሻሻ ልማድ ነው ።
ዛሬ ዛሬማ ይኸው ሰባራ ባህሪ ወደ አላህ መንገድ እጣራለሁ የሚለው አንዳንዱ ደፋርም ላይ የሚታይ ሆኗል - እጅጉን ያሳዝናል !! ቀደምት ደጋጎችን እከተላለሁ እያለ የሚሞግተው አንዳንዱ ውሸትን ሲያበዛ ማየት እንግዳ መሆኑ ቀርቷል !!
ጀሌዎቹን ለመስቀል ሀሰትን እንደ ጠመንጃ ይጠቀምበታል ። በጠላትነት የፈረጃቸውን ለመገንደስ ባልዋሉበት ያውላል - ያሳዝናል !!!
ሁሉም አላህ ፊት ይቆማል !
አንተ በሰዎች ላይ የምትዋሽ ሆይ ! እያንዳንዱ ተገቢ ዋጋውን በሚያገኝበት ቀን የዋሸህባቸው ሰዎች ከመልካም ስራህ እንደሚወስዱ አለያም ከወንጀላቸው እንደምትሸከም አስታውስ !! አላህን ፍራ !!
አላህን ፍሪ !!
በርግጥ ነው ለቡድንተኝነት ትግላቸው ሆን ብለው ውሸትን እንደ መሳሪያ ከሚገለገሉበት ሰዎች ጋር “ አላህን ፍሩ “ ማለት የሚያግባባ ቋንቋ ላይሆን ይችላል ….. የተባለውን ሁሉ ሳያጣሩ በየዋህነት የሚያወሩትን ግን ይጠቅማል ብየ ተስፋ አደርጋለሁ ። አላህን እንፍራ !!
አላህ ከውሸት ይጠብቀን !!
https://hottg.com/Muhammedsirage
>>Click here to continue<<