በራሳችን ማንነትና በስብዕናችን ላይ ለውጥ ማምጣት እና በህይወታችንና በኑሮዎችን ውስጥ ማደግ አለብን። ምንም እንኮን በዙሪያችን ያለንበት ሁኔታና ደረጃ፣ የማሃበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶቻችን የቱንም ያህል ቢሆኑም በነዚህን ውጫዊ ሁኔታዎች በመዋጥ ያለንባቸው ሁኔታዎች የኛን ማንነትና ህይወት እንዲቀርጽና እንዲቆጣጠሩን ከመፍቀድ ይልቅ ያለንበትን ሁኔታ፣ አካባቢያችንን፣ እና ዙሪያችንን መለወጥና መቅረጽ ያለብን እኛው እራሳችን ነን። ለዚህ ደግሞ ከምናያቸውና ከሚገጥሙን ውጫዊ ሁኔታዎች/ክስተቶች ሃሳባችንንና ስሜታችንን በመግዛት እና እራሳችንን በመቆጣጠር መለወጥ የምንፈልገውን ነገር ለመቅረጽና ለመፍጠር ወደ ፊት መራመድ ግድ ነው።
>>Click here to continue<<