ዛሬ ላይ ብዙ ሀብቶች የሀሳብ፣ የጭንቀትና የሰላም ማጣት ምንጭ ሆነዋል፤ ሰው ዉድ መኪና ይዞ ወጥቶ እንዳይሰረቅብኝ የት ላቁም ብሎ ይብሰለሰላል፣ ስለ ደህንነቷ ይጨነቃል፡፡
ሞላም ጎደለ ዱንያ ላይ እንከን የሌለው ነገር የለም፡፡ ካለህ ብዙ አትፈንጥዝ፤ ከሌለህም ብዙ አትተክዝ፡፡
ጠንክረህ ሥራ። አላህን የሰው እጅ ከማየት የሚጠብቅህን ያህል ሪዝቅ ለምነው፤ ጤናን ለምነው፡፡
ሆስፒታል ከሚተኙበት የስፖንጅ ፍራሽ ይልቅ እቤት የሚተኙበት የገለባ ፍራሽ ምርጥ ነው፤ ታመህ ትንፋሽህ ከሚያጥር ሪዝቅህ ቢያጥር ይሻላል፡፡
ወዳጄ! ያለህበት ሁኔታ የቱን ያህል ቢከፋም ካንተ በባሰ ሁኔታ ዉስጥ ያለ ሰው መኖሩን ላፍታም ቢሆን እንዳትዘነጋ፡፡ ከሁሉም በላይ በአላህ ተደሰት፡፡ እሱን ካለህ አህያህን ቆስቁሰህ ዉጣ፡፡ መንገድ ላይ የምታገኘዉን ሁሉ በሙሉ ፈገግታ ሰባሐል ኸይር በል።
ሰባሐል ኸይር ❤️
ይለናል ውዱ መካሪያችን መሀመድ ሰኢድ Abx
>>Click here to continue<<