TG Telegram Group & Channel
🌻ግእዝ🌻 🌻Tube🌻 | United States America (US)
Create: Update:

ማስረጃ 2:-  በዮሐ. 3:5 ላይ "ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግስት ሊገባ አይችልም።" የተባለው በውኃ ስለሚፈፀመው ጥምቀት እንጅ በምሳሌነት መንፈስ ቅዱስን ለማለት የተጠቀሰ አይደለም።

ይህን ለመረዳት ጌታችን ይህን ለኒቆዲሞስ ሲነግረው "ውኃ" የተባለው በውኃ ስለሚፈጸመው ጥምቀት  ውጪ  ሌላ ትርጉም ቢኖረው ኖሮ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ  አብራርቶ በጻፈልን ነበር። ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን ሲጽፍ የተሳሳቱ ወይም ግራ የሚያጋቡ ሃሳቦች ሲኖሩ አስተካክሎ አርሞ ያልፋል እንጂ እንዲሁ አይተወውም። "...እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር" ዮሐ. 2:19-21፤ "...ስለ አብ እንደ ነገራቸው አላስተዋሉም።" ዮሐ.8:25-27 "እንቅልፍ ስለመተኛት የተናገረ መስሏቸው ነበር" ዮሐ. 11፡13:: "የአትክልት ጠባቂ መስሏት ነበር" (ዮሐ. 21፡33)  በማለት አብራርቶ ስሕተትም ካለ አርሞ የሚጽፍ ሐዋርያ ነው።

ስለዚህም ከላይ 'ውኃ' የተባለው "መንፈስ ቅዱስ" ቢሆን ኖሮ በዮሐ. 7:37-39 ላይ እንደሰፈረው አብራርቶ ይጽፍልን ነበር።
በዮሐ. 7:38 ላይ "የሕይወት ውሃ"  የተባለው መንፈስ ቅዱስ መሆኑን አብራርቶ ገልጾ ነበርና።

ማስረጃ 3:-
በዮሐ. 3:5 ላይም የተጻፈው በቀጥታ በውኃ ስለሚፈጸመው ጥምቀት ባይሆን ኖር አብራርቶ ይገልጸው ነበር። "በውኃና በመንፈስ"  የተባለው በቀጥታ በውኃ ስለመጠመቅ እንጂ ስለ መንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ሆኖ አለመቅረቡን ለመረዳት:-

1ኛ.  በዮሐ. 4:10-14 እና በዮሐ. 7:38-39 ላይ የሕይወት ውኃ (living water) እያለ ሲናገር በዮሐ. 3:5 ላይ ግን "ውኃ" በማለት ብቻ ነው የተባለው። ስለ መንፈስ ቅዱስ ሲናገር የሕይወት ውሃ እያለ ሲገልጸው በዮሐ.3:5 ላይ ደግሞ "ውኃ" ብቻ በማለት ምሳሌያዊ እንዳልሆነ ያስረዳናል።

2ኛ. በዮሐ. 4:10-14 እና በዮሐ. 7:37-39 ላይ በውኃና በሕይወት ውኃ (living water) መካከል በማነጻጸር ሲያስቀምጥ በዮሐ. 3:5 ግን እያነጻጸረ አልገለጸም ምክንያቱም "በውኃና በመንፈስ" በማለት የተገለጸው ምሳሌያዊ ሳይሆን በቀጥታ በውኃ ጥምቀት የሚፈጸመውን የሚያመለክት ነውና።

3ኛ. "በውኃና በመንፈስ" የተባለው ላይ "ውኃ" የተባለው ዮሐ. 7:38-39 ላይ "የሕይወት ውኃ" ተብሎ እንደተገለጸው መንፈስ ቅዱስን ለማመልከት ቢሆን ኖሮ "እና" በሚል አያያዥ ቃል ባልተጠቀመ ነበር። ምክንያቱም ውኃ የተባለው መንፈስ ቅዱስ ቢሆን ኖሮ "በውኃና በመንፈስ" በማለት አይገልጽም ነበር። ድግግምሽ ይሆናልና። ይልቁኑ በውሃና በመንፈስ የተባለው በጥምቀት የመንፈስ ቅዱስ ልጅነትን የምናገኝበትን የሚያመለክት ቃል ነው።


ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]

ማስረጃ 2:-  በዮሐ. 3:5 ላይ "ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግስት ሊገባ አይችልም።" የተባለው በውኃ ስለሚፈፀመው ጥምቀት እንጅ በምሳሌነት መንፈስ ቅዱስን ለማለት የተጠቀሰ አይደለም።

ይህን ለመረዳት ጌታችን ይህን ለኒቆዲሞስ ሲነግረው "ውኃ" የተባለው በውኃ ስለሚፈጸመው ጥምቀት  ውጪ  ሌላ ትርጉም ቢኖረው ኖሮ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ  አብራርቶ በጻፈልን ነበር። ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን ሲጽፍ የተሳሳቱ ወይም ግራ የሚያጋቡ ሃሳቦች ሲኖሩ አስተካክሎ አርሞ ያልፋል እንጂ እንዲሁ አይተወውም። "...እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር" ዮሐ. 2:19-21፤ "...ስለ አብ እንደ ነገራቸው አላስተዋሉም።" ዮሐ.8:25-27 "እንቅልፍ ስለመተኛት የተናገረ መስሏቸው ነበር" ዮሐ. 11፡13:: "የአትክልት ጠባቂ መስሏት ነበር" (ዮሐ. 21፡33)  በማለት አብራርቶ ስሕተትም ካለ አርሞ የሚጽፍ ሐዋርያ ነው።

ስለዚህም ከላይ 'ውኃ' የተባለው "መንፈስ ቅዱስ" ቢሆን ኖሮ በዮሐ. 7:37-39 ላይ እንደሰፈረው አብራርቶ ይጽፍልን ነበር።
በዮሐ. 7:38 ላይ "የሕይወት ውሃ"  የተባለው መንፈስ ቅዱስ መሆኑን አብራርቶ ገልጾ ነበርና።

ማስረጃ 3:-
በዮሐ. 3:5 ላይም የተጻፈው በቀጥታ በውኃ ስለሚፈጸመው ጥምቀት ባይሆን ኖር አብራርቶ ይገልጸው ነበር። "በውኃና በመንፈስ"  የተባለው በቀጥታ በውኃ ስለመጠመቅ እንጂ ስለ መንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ሆኖ አለመቅረቡን ለመረዳት:-

1ኛ.  በዮሐ. 4:10-14 እና በዮሐ. 7:38-39 ላይ የሕይወት ውኃ (living water) እያለ ሲናገር በዮሐ. 3:5 ላይ ግን "ውኃ" በማለት ብቻ ነው የተባለው። ስለ መንፈስ ቅዱስ ሲናገር የሕይወት ውሃ እያለ ሲገልጸው በዮሐ.3:5 ላይ ደግሞ "ውኃ" ብቻ በማለት ምሳሌያዊ እንዳልሆነ ያስረዳናል።

2ኛ. በዮሐ. 4:10-14 እና በዮሐ. 7:37-39 ላይ በውኃና በሕይወት ውኃ (living water) መካከል በማነጻጸር ሲያስቀምጥ በዮሐ. 3:5 ግን እያነጻጸረ አልገለጸም ምክንያቱም "በውኃና በመንፈስ" በማለት የተገለጸው ምሳሌያዊ ሳይሆን በቀጥታ በውኃ ጥምቀት የሚፈጸመውን የሚያመለክት ነውና።

3ኛ. "በውኃና በመንፈስ" የተባለው ላይ "ውኃ" የተባለው ዮሐ. 7:38-39 ላይ "የሕይወት ውኃ" ተብሎ እንደተገለጸው መንፈስ ቅዱስን ለማመልከት ቢሆን ኖሮ "እና" በሚል አያያዥ ቃል ባልተጠቀመ ነበር። ምክንያቱም ውኃ የተባለው መንፈስ ቅዱስ ቢሆን ኖሮ "በውኃና በመንፈስ" በማለት አይገልጽም ነበር። ድግግምሽ ይሆናልና። ይልቁኑ በውሃና በመንፈስ የተባለው በጥምቀት የመንፈስ ቅዱስ ልጅነትን የምናገኝበትን የሚያመለክት ቃል ነው።


ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]


>>Click here to continue<<

🌻ግእዝ🌻 🌻Tube🌻




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)