ውጤታማ የተልዕኮ አፈፃፀማችንን የሥነ ምግባር ጥሰትን ፣ ብልሹ አሠራር እና ሙስናን በመከላከል ልንደግም ይገባል
ሌተናል ጄኔራል አጫሉ ሸለመ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ሞ
የመከላከያ ሥነ ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት ከሁሉም የተቋሙ ክፍሎች የሥነ ምግባር መከታተያ አመራሮች ጋር ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ውይይት አድርጓል።
በማጠቃለያው መርሀ ግብር በክብር እንግድነት የተገኙት የመከላከያ ሰው ሃብት አመራር ዋና መምሪያ ሀላፊ ሌተናል ጄኔራል አጫሉ ሸለመ ዳይሬክቶሬቱ ተቋሙና ሠራዊቱ የሥነ ምግባር ስህተትንና ብልሹ አሠራርን እየታገለ ተልዕኮውን በብቃት እንዲወጣ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ብለዋል ።
ሠራዊቱ የሀገራዊ ተልዕኮው ውጤታማነትን በሥነ ምግባር ክፍተት ፣ ሙስናና ብልሹ አሠራርን በመታገል መድገም ይገባል ያሉት ጄኔራል መኮንኑ ቀጣይም በሥልጠና ፣ በሃብት ምዝገባና በሌሎችም የተገኘውን ውጤትና ዕውቀት በማካፈል በቅንነትና በታማኝነት ሀገርን ማገልገል እንደሚገባ አሳስበዋል።
ሁሉም የተቋሙ አባላት የሙስና ወንጀሎችን በማወቅ ሀገርንና ተቋሙን ከሙስና ስጋት መጠበቅ የሚችልና አምርሮ የሚጠላ በማድረግ ቀጣይም ተልዕኮውን
ለመፈፀም እንጥራለን ብለዋል የመከላከያ ሥነ ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮሎኔል አዲሱ ሽፈራው ።
ኮሎኔል አዲሱ ዳይሬክቶሬቱ በሥልጠና ፣ በሃብት ምዝገባና በሌሎች ላገኘው ውጤት ድጋፍ ላደረጉ የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን እና ለተቋሙ ክፍሎች ምስጋና አቅርበው ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የመስራቱን ሂደት እንደሚያጠናክሩም ተናግረዋል።
የመከላከያ ሥነ ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት በበጀት ዓመቱ ድጋፍ ላደረጉና የተሻለ የሥራ አፈፃፀም ለነበራቸው ክፍሎች እውቅናና ሰርተ-ፊኬት አበርክቷል።
ዘጋቢ ቃለእግዚአብሔር ፍቃዱ
ፎቶግራፍ ፉራ አብደላ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://hottg.com/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official
>>Click here to continue<<
