TG Telegram Group & Channel
ስብዕናችን #Humanity | United States America (US)
Create: Update:

🔴ብርጭቆህን ባዶ አድርግ!!

ቻይና ውስጥ አንድ በጣም ጠቢብ የዜን ፍልስፍና (Zen Philosophy) መምህር ነበር።  ሰዎች የእርሱን እርዳታ ለማግኘት እና ጥበብ ለመቅሰም  ብዙ ኪሎ ሜትሮችን ይጓዙ ነበር።  

አንድ ቀን አንድ የተማረ (ምሁር) ምክር ለማግኘት መምህሩን ይጎበኛል።   ምሁሩም ስለ ዜን የህይወት ፍልስፍና ለመማር እንደመጣ ይናገራል።

🔹ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ውይይቱ ተጀመረ። ምሁሩ አእምሮው ‘በሁሉን አውቃለሁ ባይነት’ የተሞላ እና በእራሱ አመለካከት፣ አስተሳሰብ  እና እውቀት ፍፁምነት  ያምን ነበርና በንግግራቸው ወቅት መምህሩ የሚናገረውን እና የሚያስተምረውን ከመስማት እና ትኩረት ከመስጠት ይልቅ የራሱን ታሪክ እና ስለ ምሁርነቱ በማውራት መምህሩን የመናገር እድል ይነሳዋል። 

🔹መምህሩም በእርጋታ አንድ ላይ ሻይ እንዲጠጡ ሐሳብ ያቀርባል። ለእንግዳው (ምሁሩ) ባቀረበው ብርጭቆም ሻይ ይቀዳለታል።  ብርጭቆው ሞላ። 

🔹ነገር ግን መምህሩ እየፈሰሰም ቢሆን ሻይውን መቅዳቱን አላቆመም። ጠረጴዛው ላይ እስኪፈስ ድረስ ሻይ እየቀዳለት ነበር።  ሻይው ወለሉ ላይ ብሎም በምሁሩ ጃኬት ላይም ይፈስ ነበር።   ምሁሩም በመገረም እየተመለከተው ‘’“ተው እንጅ!  ብርጭቆው እኮ ሞልቷል።  ማየት አትችልም እንዴ ” ይላል።

🔸መምህሩ በፈገግታ “ብርጭቆህን ባዶ አድርግ! አንተም  ልክ እንደዚህ ብርጭቆ ሁሉ አእምሮህ ባረጁ ሃሳቦች እና እምነቶች የተሞላ ስለሆነ ከዚህ በላይ ምንም አዲስ እውቀትና ሃሳብ መቀበል አቁመሃል። ‘’ በማለት ተናግሮ ብርጭቆውን ባዶ አድርጎ እንዲመለስ መከረው።  .

እኛም በህይወታችን ውስጥ በየቀኑ ተመሳሳይ ታሪክ ይከሰታል። ሁሉንም የምናውቅ ይመስለናል እናም ‘በትህትና ማዳመጥ እንዲሁም ከሌሎች መማር አያስፈልገንም!’ ብለን አእምሮአችንን ሞልተን ባዶ ማድረግ አቅቶናል!!!

🟢In Zen we don't Find the Answer , We loose the question" የምትል ግሩም አባባል አላቸው። ራስህን ባዶ አርገህ መማር ከፈለክ ዙሪያህ ሁሉ አስተማሪ ነው!  ሩቅ ሳትሄድ ከጎንህ ላለው ሰው ልብህን ክፈት፣ በመጠየቅ በመመለስ ሳይሆን በመረዳት እና በማስተዋል ነው አብርሆት የሚፈጠረው።

🟡የሰው ልጅ የነብሱን መንፈሳዊ ጎዳና ትክክለኝነት ማወቅ የሚችለው መንገደኛው ራሱ ነው..ስለ ሕይወትህ ችግር ከገጠመህ ወይም ጥያቄ ከተፈጠረብህ ዙርያህን አጥና... ያለህበት ሁኔታ ከሕይወትህ ጋር ያለውን አንድምታ መርምር በተለይ ትንሽ ትልቅ ሳትል በአቅራብያህ ያሉ ሰዎችን ህይወት በመመልከት ላንተ ምን መልእክት እንዳለው በትጋት ተከታተል ምክንያቱም የተፈጥሮ መንፈሳዊ አንደበት ናቸውና..."

🔴የተፈጥሮን መንፈሳዊ ቋንቋ ተማር ስትወድቅ ሆነ ስትነሳ ፍቺው ምን እንደሆነ ውስጥህን ጠይቅ  እውቀትን ሩቅ ፍልስፍና ወይም አንቃቂ ዲስኩሮች ውስጥ አትፈልግ፣ ከራስህ ጀምር ምክንያቱም የኩራዝ ብርሃንን ብታይ በደንብ የሚያበራው አቅራብያው ላለው ነው። አንተም ለራስህ ብርሀን ሁን መማር አታቁም፣ እድገትህን አትግታ፣ እራስህን አሻሽል፤  በአዳዲስ እውቀቶች እራስህን አንፅ!

ሁሌም ብርጭቆህን ባዶ አድርገህ ተነስ!

        ውብ ቅዳሜ ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot

🔴ብርጭቆህን ባዶ አድርግ!!

ቻይና ውስጥ አንድ በጣም ጠቢብ የዜን ፍልስፍና (Zen Philosophy) መምህር ነበር።  ሰዎች የእርሱን እርዳታ ለማግኘት እና ጥበብ ለመቅሰም  ብዙ ኪሎ ሜትሮችን ይጓዙ ነበር።  

አንድ ቀን አንድ የተማረ (ምሁር) ምክር ለማግኘት መምህሩን ይጎበኛል።   ምሁሩም ስለ ዜን የህይወት ፍልስፍና ለመማር እንደመጣ ይናገራል።

🔹ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ውይይቱ ተጀመረ። ምሁሩ አእምሮው ‘በሁሉን አውቃለሁ ባይነት’ የተሞላ እና በእራሱ አመለካከት፣ አስተሳሰብ  እና እውቀት ፍፁምነት  ያምን ነበርና በንግግራቸው ወቅት መምህሩ የሚናገረውን እና የሚያስተምረውን ከመስማት እና ትኩረት ከመስጠት ይልቅ የራሱን ታሪክ እና ስለ ምሁርነቱ በማውራት መምህሩን የመናገር እድል ይነሳዋል። 

🔹መምህሩም በእርጋታ አንድ ላይ ሻይ እንዲጠጡ ሐሳብ ያቀርባል። ለእንግዳው (ምሁሩ) ባቀረበው ብርጭቆም ሻይ ይቀዳለታል።  ብርጭቆው ሞላ። 

🔹ነገር ግን መምህሩ እየፈሰሰም ቢሆን ሻይውን መቅዳቱን አላቆመም። ጠረጴዛው ላይ እስኪፈስ ድረስ ሻይ እየቀዳለት ነበር።  ሻይው ወለሉ ላይ ብሎም በምሁሩ ጃኬት ላይም ይፈስ ነበር።   ምሁሩም በመገረም እየተመለከተው ‘’“ተው እንጅ!  ብርጭቆው እኮ ሞልቷል።  ማየት አትችልም እንዴ ” ይላል።

🔸መምህሩ በፈገግታ “ብርጭቆህን ባዶ አድርግ! አንተም  ልክ እንደዚህ ብርጭቆ ሁሉ አእምሮህ ባረጁ ሃሳቦች እና እምነቶች የተሞላ ስለሆነ ከዚህ በላይ ምንም አዲስ እውቀትና ሃሳብ መቀበል አቁመሃል። ‘’ በማለት ተናግሮ ብርጭቆውን ባዶ አድርጎ እንዲመለስ መከረው።  .

እኛም በህይወታችን ውስጥ በየቀኑ ተመሳሳይ ታሪክ ይከሰታል። ሁሉንም የምናውቅ ይመስለናል እናም ‘በትህትና ማዳመጥ እንዲሁም ከሌሎች መማር አያስፈልገንም!’ ብለን አእምሮአችንን ሞልተን ባዶ ማድረግ አቅቶናል!!!

🟢In Zen we don't Find the Answer , We loose the question" የምትል ግሩም አባባል አላቸው። ራስህን ባዶ አርገህ መማር ከፈለክ ዙሪያህ ሁሉ አስተማሪ ነው!  ሩቅ ሳትሄድ ከጎንህ ላለው ሰው ልብህን ክፈት፣ በመጠየቅ በመመለስ ሳይሆን በመረዳት እና በማስተዋል ነው አብርሆት የሚፈጠረው።

🟡የሰው ልጅ የነብሱን መንፈሳዊ ጎዳና ትክክለኝነት ማወቅ የሚችለው መንገደኛው ራሱ ነው..ስለ ሕይወትህ ችግር ከገጠመህ ወይም ጥያቄ ከተፈጠረብህ ዙርያህን አጥና... ያለህበት ሁኔታ ከሕይወትህ ጋር ያለውን አንድምታ መርምር በተለይ ትንሽ ትልቅ ሳትል በአቅራብያህ ያሉ ሰዎችን ህይወት በመመልከት ላንተ ምን መልእክት እንዳለው በትጋት ተከታተል ምክንያቱም የተፈጥሮ መንፈሳዊ አንደበት ናቸውና..."

🔴የተፈጥሮን መንፈሳዊ ቋንቋ ተማር ስትወድቅ ሆነ ስትነሳ ፍቺው ምን እንደሆነ ውስጥህን ጠይቅ  እውቀትን ሩቅ ፍልስፍና ወይም አንቃቂ ዲስኩሮች ውስጥ አትፈልግ፣ ከራስህ ጀምር ምክንያቱም የኩራዝ ብርሃንን ብታይ በደንብ የሚያበራው አቅራብያው ላለው ነው። አንተም ለራስህ ብርሀን ሁን መማር አታቁም፣ እድገትህን አትግታ፣ እራስህን አሻሽል፤  በአዳዲስ እውቀቶች እራስህን አንፅ!

ሁሌም ብርጭቆህን ባዶ አድርገህ ተነስ!

        ውብ ቅዳሜ ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot


>>Click here to continue<<

ስብዕናችን #Humanity




Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)