#Injury_update
አርሰናል በሳምንቱ መጨረሻ ከማንችስተር ሲቲ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ በጉዳት ላይ የነበሩ ተጨዋቾቹን መልሶ የሚያገኝ ይሆናል።
ለእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ተጠርቶ ምንም ሳይጫወት ለጥንቃቄ ወደ ቡድኑ የተመለሰው ቡካዮ ሳካ እና ብራዚላዊው የተከላካይ መስመር ተጨዋች ጋብሬል ማግሀሌስ ለእሁድ ከባድ ፍልሚያ የመድረስ እድላቸው ሰፊ መሆኑ ተነግሯል።
አርሰናል ሼፍልድ ዩናይትድን 6 - 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ላይ ጉዳት አስተናግዶ የነበረው ጋብሬል ማርቲኔሊ ለጨዋታው የመድረስ እድል ቢኖረውም ነገር ግን ቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ የመጀመር እድሉ ጠባብ እንደሆነ ተነግሯል። [ Mo Arsenal ]
SHARE @ETHIO_ARSENAL
>>Click here to continue<<