ከማንም አልበልጥም፣ ከማንም አላንስም!
በተፈጥሮ “ሰው’ ነት” - ከማንም አልበልጥም ከማንም አላንስም!
በዘርና በቋንቋ - ከማንም አልበልጥም፣ ከማንም አላንስም!
በመልክና በቁመና - ከማንም አልበልጥም፣ ከማንም አላንስም!
በቆዳ ቀለም - ከማንም አልበልጥም፣ ከማንም አላንስም!
በእነዚህ ከላይ በተጠቀሱት የፈጣሪ ስጦታዎች አማካኝነት በማንም ላይ የበላይነት፣ ከማንም ስርም የበታችነት ከተሰማኝ በራሴ ላይ ያለኝ አመለካከት ላይ መስራት እንደሚገባኝ ጠቋሚ ነው፡፡
ከሌላው ሰው የመብለጥና የማነስ ሁኔታ ሊከሰት ከቻለ፣ ሊሆን የሚችለው በሶስት ነገሮች ምክንያት ነው፡-
1. ባሳደኩትና በየእለቱ በማሳየው መልካም ወይም መጥፎ ባህሪይ አማካኝነት የበላይ ወይም የበታች ልሆን እችላለሁ፡፡
2. የእኔን፣ የቤተሰቤንና የሕብረተሰቤን ሕይወት ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ በማከናውናቸው ወይም ችላ በምላቸው ተግባሮቼ አማካኝነት የበላይ ወይም የበታች ልሆን እችላለሁ፡፡
3. ባዳበርኩት ወይም ችላ ባልኩት የሕይወት ዲሲፕሊን አማካኝነት የበላይ ወይም የበታች ልሆን እችላለሁ፡፡
ከራሳችን አልፈን ለሌሎች የሚተርፍ ሕይወት ውስጥ ለመግባት ካስፈለገ ትርጉም የለሹንና የውሸቱን የበላይነትና የበታችነት ስሜት ተወት በማድረግ በእርግጥም ተሽለን እንድንገኝ በሚያደርግን ልማድና ልምምድ ላይ እናተኩር፡፡
https://hottg.com/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/
>>Click here to continue<<
