ውድ የዲላ ሀይኪንግ ቤተሰቦች ለነገ ጉዟችን እንደተዘጋጃሁ ተስፋ እናደርጋለን። ለጉዞ ሲመጡ እነዚህን ነጥቦች ልብ ይበሉ ፦
1. መታወቅያ መያዝዎን አይዘንጉ። መታወቅያ ያልያዘ ሰው በጉዞው ላይ የማናስተናግድ ሲሆን መታወቅያ ሳይዙ መተው ለሚፈጠረው መጉላላት ሀላፊነት አንወስድም።
2. ከቤትዎ ሲወጡ ምቾት የማይነሳዎትን ቀለለ ያለ ምግብ ይመገቡ።
3. የጉዞ ሰአታችን 12 ከ 45 ሲሆን ሊፈጠሩ ለሚችሉ አንዳንድ ችግሮች ተጨማሪ 15 ደቂቃ ይዘናል። 1 ከ 00 ሲሆን ጉዟችንን ከማዞርያ መድህን ህንፃ ስር እንጀምራለን። ከዚህ ሰአት ኋላ ለሚመጡ ቤተሰቦቻችን ሀላፊነት ስለማንወስድ ሰአትዎን ያክብሩ።
4. ለጉዞዎ አመቺ የሆኑ ልብስ ያድርጉ፤ ለእንቅስቃሴ አመቺ የሆነ መጫምያ ማድረግዎንም ልብ ይበሉ።
5. በጉዞዎ ላይ ለትውስታ ፎቶ ያንሱና ያጋሩን!
ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በ
0902946142 - @beka_baba
0961379810 - @SanGiliy
ጋር ይደውሉ።
>>Click here to continue<<