ዛሬ ቅዳሴ ላይ ከተነበበው የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክት:
“በአንዱም[በአዳም] በደል ሞት በአንዱ በኩል ከነገሠ፥ ይልቁን የጸጋን ብዛትና የጽድቅን ስጦታ ብዛት የሚቀበሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሕይወት ይነግሣሉ።”
[ሮሜ 5: 17]
ሁለት ዓይነት ሕይወት አለ.. አዳማዊ እና ክርስቶሳዊ ማለት ነው።
አዳማዊ:- አንዱ አዳም ሃጢአትን ሠራ በሃጢአቱም ሞት መጣ ይህም ሞት ከአዳም በሥጋ ለሚከፈሉ ሁሉ ደረሰ። አዳምን መስለው እንደ አዳም ሃጢአትን እየሰሩ የሚኖሩ ሃጢአት በሥጋቸው ላይ የሰለጠነባቸው ሆኑ። ይህ አዳማዊው ኑሮ ነው፤ በአዳም በኩል ሞት።
ክርስቶሳዊ:- ክርስቶስ ደግሞ ጽድቅን ሁሉ በመፈጸም ስለ ሁላችን ሞቶ በመነሣቱ በእርሱ አምነው የሚጠመቁ ሁሉ ከእርሱ ጋር አንድ በመሆን ከአዳማዊው ሞት በክርስቶስ በኩል ወደ ሆነው ሕይወት ይሸጋገራሉ። ከዚያም ኢየሱስ ጽድቅን ሁሉ ስለፈጸመ እነዚህም በቅድስና እየተመላለሱ እንደ እርሱ ይኖራሉ። ይህ ክርስቶሳዊው ኑሮ ነው፤ በክርስቶስ በኩል ሕይወት።
መልካም የጌታ ቀን
@Apostolic_Answers
>>Click here to continue<<