ችግራችንን ካላወቅነው መፍትሄ አናገኝም..
ብዙዎቻችን ክርስቲያኖች ከእግዚአብሔር እንደራቅንና ወንጌልም መዳረስ ባለበት ልክ ለራሳችንም እንዳልተዳረሰ እኮ ማንም መጥቶ ሊነግረን አያስፈልገንም በቃ በግልጽ የሚታይ ነው.. መሠረታዊውን ትምህርት የሚያውቅ ምን ያህል ሰው ነው..?? የንስሐ አባት ይዞ በንስሐ የሚመላለስ ምን ያህል ሰው ነው..?? ከቅዱስ ምስጢር የሚካፈል ምን ያህል ሰው ነው..?? ጌታ ኢየሱስን ከልቡ እንደው የሚወደውና የሚታዘዘው ምን ያህል ሰው ነው..??
“ሚካኤል ሲባል ይደምቃል ኢየሱስ ሲባል ከሚደምቀው ይልቅ” የሚለውን ክርክር ትተነው በቃ ራሳችን ላይ እንስራ.. ያሉብንን ድክመቶች መካድ ማለት ድክመቶችን ላለመቅረፍ ወስኖ እንደመቀመጥ ነው.. እና ሁሉም በየቤቱም በየሚዲያውም እንደተሰጠው መጠን ሥራ መስራት ነው ያለበት.. ከዛ ከተወሰኑ ጊዜያት በኋላ ሚገርም ለውጥ እናመጣለን ራሳችን ላይ.. የማያከራክር ነገር አያከራክረን😁😁 መፍትሄው ላይ እናተኩር
@Apostolic_Answers
>>Click here to continue<<