አሳባችሁን እስቲ ልወቀው..
የሴቶች እና ሕጻናት ጥቃት ላይ ሚሠራ የራሳችን ክርስቲያናዊ የሆነ ስብስብ ቢኖረንስ..?? መልካም ሥነምግባር ያላቸው ሰዎች እንዲበዙ ሃሪፍ ከሆነ.. እና ደግሞ ከክርስቲያን ሰዎች ሲሆን ደግሞ ተቀባይነትም ይኖረዋል ብዬ አስባለሁ ምክንያቱም እምነታቸውን በማይጋጭ መልኩ ስለሚያደርጉት..
- በዛው ደግሞ አንድ በጣም ጥቅም ያለው ነገር ቢደረግ ብዬ ማስበው.. አንዳንድ እህቶች በቤተ ክርስቲያን ሰዎች አላስፈላጊ ነገር ሲደርስባቸው በማፈርም ዝም ነው ሚሉት እና ለሚኖረን ግሩፕ የሚናገሩ ይሆናል.. ግሩፑ ደግሞ ወደ ቤተ ክርስቲያንም ወደ ሕግም መሄድ ካለበት እንዲሄድ ያደርጋል.. ይህ ነገር እንዳለ ከተሰማ ይህንን ድርጊት የሚፈጽሙ የቤተ ክርስቲያን ሰዎችም አርፈው ይቀመጣሉ ብዬ አስባለሁ.. በዚህም እንጥቀም እስቲ የምንችል ሰዎች..
ያው ግን እስቲ ሚሆን ከሆነ እዚህ ጉዳይ ላይ በጣም መሥራት የሚፈልጉና ባለሙያ የሆኑ ሰዎች ያስፈልጉናል ያው እኔ እዚህ ላይ ምንም ልሰራ አልችልም ምናልባት የክርስትናን ነገር ከማስተማርና እነሱን ከማስተዋወቅ ውጪ
>>Click here to continue<<