አንዳንዴ በበሽታ ተጠቅተን ምናምን ግን ደግሞ በሽታውን ሳናውቀው ለጊዜውም የህመም ስሜት ሳይሰማን በብዙ ውስጣችን ሊጎዳ ይችላል..
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም እንደዛ እየሆነች ነው.. ብዙ ሕዝብ ይዛለች ምናምን እና በዛ ምክንያት ሰላም ሊመስል ይችላል ግን ደግሞ ሕዝቦቿ በአብዛኛው ከንስሐ ሕይወትና ከቅዱስ ቁርባን የራቅን.. ቤተሰብ ስንመሰርት ስናገባ እንኳ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ውጪ ያለ ቅዱስ ቁርባን.. በአጭሩ የልምድ ብቻ ክርስቲያን ሆነናል..
እረኛ እንኳ ብዙም የላት.. ያሉት በዘር እና በገንዘብ የተተበተቡና ሰው ሲጋደል ራሱ ግድ ማይላቸው.. የምእመናን የድኅነት ጉዳይ ግድ ማይሰጣቸው ይመስላሉ.. ምን አለፋአችሁ ቤተ ክርስቲያን በጣም አደጋ ውስጥ ናት..
ስለዛ በዚህ ጊዜ ሁላችን በያለንበት የራሳችንን ሃላፊነት እንወጣ.. ጌታ ይርዳን..
@Apostolic_Answers
>>Click here to continue<<