ዛሬ ቅዳሴ ላይ ከተነበበው የቅዱስ ወንጌል ክፍል:
የዮሐንስ ወንጌል 14
1፤ ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ።
2፤ በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤
.
.
.
6፤ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።
- ለዘላለም የምንኖርበት በአብ ዘንድ መኖሪያ አለን.. ይህ ትልቅ ተስፋ ነው.. አዲሱ ሁሌም አዲስ የሚሆነውም የማያልቀው ሕይወት ከፊታችን አለ..
- ጌታ ኢየሱስ ደግሞ መንገዳችን ከሆነ እርሱ እውነትም ከሆነ ራሱ ደግሞ ሕይወትም ከሆነ እንግዲያውስ ኢየሱስን ይዘን ልባችን አይታወክ አንፍራ.. በዚህ መንገድ የሚሄድ ይህንን እውነት የያዘ ይህንን ሕይወት ያገኘ ሁሉ በአብ ቤት ለዘላለም ይኖራል..
- በኢየሱስ መንገድ የምንሄደው ግን የእርሱን ፈለግ በመከተል በቅድስና ሕይወት ሊሆን ይገባዋል.. ከቅዱስ ምስጢር ያልራቀ ፍሬ ያለበት ሕይወት..
መልካም የጌታ ቀን
@Apostolic_Answers
>>Click here to continue<<