TG Telegram Group Link
Channel: ወጣቱ ና ሙዱ
Back to Bottom
👉የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ለሆናችሁ የቻናላችን ቤተሰቦች እንዲሁም ለመላው ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ መውሊድ በዐል በሰላም አደረሳችሁ።
ጠቃሚ ምክር ለሴቶች

እኔና ባሌ አራት አመታትን በፍቅር ኖራናል በትዳር ደግሞ 4 አመታትን ትዳርና ፍቅር የተለያየ ነው እያልኩ አይደለም እኔና ባሌ ከትዳር በሓላ ጥሩ የፍቅር ህይወት አልነበረንም ለዛ ነው ባሌ በጣም ዝምታኛ ነው ምንም ነገር አጥፊቼ ብሆን አይቶ ዝም ይላል ። ስለዚህ የበላይነት ይሰመኝ ጀመረ ጓደኞቼም ጀግና እንደሆንኩ መሰከሩ ታዲያ ኩራቴ የበለጠ ጨመረ ለባሌ ምንም አይነት ክቡር መስጠት አቆምኩ ። የትም ውዬ ማታ ላይ እመጣለሁ ባሌ በጣም ተናዶ እንኩዋን ዝም ይላል ። ታዲያ አንድ ቀን አምሽቼ ወደ ቤት ስመጣ በጣም ተናዶ ቆይ ለምን ለትዳርሽ ክቡር አይኖርሽም የድሮ ፍቅረችን ወዴት ሄደ አለኝ እኔ ንቄ ገፍቼ ሊገባ ስል በጥፊ መታኝ ለመጀመሪያ ጊዜ በጥፊ መታኝ ለመጀመርያ ጊዜ በኔ ላይ በር ቆልፎ እሱ ቤት አደራ ጥዋት ላይ ቤተሰቦቼ መጥቶ ፖሊስ አምጥቶ እሱን እስር ቤት ወሰዱት ከዛም ከእስር ቤት አስወጥቼ የፍቺ ጥያቄ አቀረብኩ ሁሉም ሰው ትክክል ነሽ አሉ ጓደኞቼም ጥሩ አደረግሽ የት አባቱ አሉኝ ።

ከዛ እሱም በሀዘን ተሞልቶ ድርሻዬን ሰጥቶ ብቻውን ተቀመጠ ። ከሁለት ዓመት በሓላ እሱ ሌላ ሚስት አግብቶ ልጆች ወልዶ ጥሩ ህይወት እየኖረ ነው ። የኔ ህይወት ግን ተበላሸ ። ትላንት ትክክል ነሽ ያሉት ሁሉ ዛሬ ትክክል አይደለሽም አሉኝ ። ትላንት የት አባቱ ወንድ የት ጠፍቶ የሉት እነሱ ለእራሳቸው ጥሩ ህይወት እየኖሩ ነው እኔ ግን ብቻዬን ቀረሁ ትላንት ከአንቺ ጋር ነን ያሉት ሁሉ ዛሬ ከኔ ጋር የሉም እህቶቼ ሴት ልጅ በተፈጥሮ ጠቢቡ ናት የተበላሽ ትዳር ማስተካከል ትችላለች ።

ስለዚህ በትዳረችሁ ባልሽ ሞኝ ብሆን እንኩዋን አንቺ ትዳረሽን ማስተካከል ትችያለሽ በትዳር መቀልድ ግን ትልቅ አለማውቅ ነው ። ከምንም በላይ ለትዳረችሁ ክቡር ስጡ ትዳር የሴት ልጅ ውበት ነው ። በትዳረችሁ መከላከል ለሚገባ ሰው እሱ ሰው መልካም አይደለም ። ስለዚህ ከእንደዚህ አይነት ሰው እራቁ ምክሩንም አትስሙ ።
ቴሌግራምን ለመታወቅ ሳይሆን ያወቅነውን ለማሳወቅ እንጠቀም ፡፡

ማወቅ መልካም ነው ያወቁትን ማሳወቅ ደግሞ ፍፁም በጎነት ነው ፡፡ በምድር ላይ የምናደርጋቸው መልካም ነገሮች ሁሉ በሰማይ ላይ የዘላለም ደመወዝ ሆነው ይከፈሉናል ፡፡ ሁሌም ቢሆን ከክፋት ይልቅ በጎ በጎውን ነገር እናስብ መልካምነት ለራስ ነውና ፡፡

ስለዚህ አንተም ይህ አሁን ያነበብከው መጣጥፍ ትምህርት ሰጪ ሆኖ ካገኘሀው የእርስዎ ዘመዶችህ እንዲያነቡትና ትምህርት እንዲወስዱ ዘንድ ሼር ያድርጉላቸው ።
ይነበብ


በራስ መተማመንን (Self Confidence) ለማሳደግ የሚረዱ አስር ሙያዊ ምክሮች።

 ለራስዎ ያለዎት ከፍ ያለ ግምት ሌሎች እርስዎን የሚያዩበት መንገድ ጥሩ እንዲሆን ከፍተኛ ሚና አለው። በራስ የመተማመን ስሜት ሲኖርዎትም በተሰማሩበት ሥራ ላይ የበለጠ ስኬታማ እንዲሆኑ ከፍተኛ እርዳታ አለው።
ምንም እንኳን በራስ መተማመን ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩት ምክንያቶች ብዙዎቹ ከእርስዎ ቁጥጥር ውጭ ቢሆኑም፣ በራስ መተማመንን ለመገንባት የሚረዱ ብዙ ነገሮችን ማድረግ ይችላሉ። እነዚህን 10 ስትራቴጂዎች በመጠቀም ያልዎትን በራስ መተማመን ከፍ አድርገው ችሎታዎን በትክክለኛው ሁኔታ ሥራ ላይ ማዋል ይችላሉ።
👣1. አለባበስዎ ጥሩ ይሁን (Dress sharp)።
የእርስዎ አካላዊ ገጽታ እና አለባበስ ላይ ከማንም ሰው በላይ እርስዎ የቀረበ እይታ እና ግንዛቤ አለዎት። ስለሆነም፣ ጥሩ ሆነው እንደማይታዩ በሚሰማዎት ጊዜ፣ ከሌሎች ጋር የሚያደርጉት የሃሳብ ልውውጥ ሂደት ውስጥ ምቾት እንዳይሰማዎት ያደርጋል። ስለራስዎ ገፅታ ግን መልካም አመለካከት ሲኖርዎ ምቾትዎ ይጠበቅና ከሰዎች ጋር የሚያደርጉዋቸው ግንኙነቶች ላይ ልበ ሙል ይሆናል። የራስ ገፅታን ጥሩ ለማድረግ የሰውነትን እና የገላን ንፅህና መጠበቅ፣ ፀጉርን እና ፂምን በቅጡ መከርከም እንዲሁም በወቅቱ ተቀባይ የሆኑ ፋሺኖችን በማዎቅ እና አቅም በፈቀደ መልኩ መከተል ይረዳል። ይህ ማለት በልብስ ላይ ብዙ ገንዘብ ማውጣት አለብዎት ማለት አይደለም። ነገር ግን፣ ብዙ ርካሽ ልብሶችን ከመግዛት ይልቅ፣ ጥቂት የተመረጡ እና ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ዕቃዎች መግዛት አለባበስን ጥሩ ለማድረግ ከመርዳታቸውም በላይ ለረጅም ጊዜ ዘመናዊ ሆነው እንዲቆዩ ስለሚያደርጉ ረዘም ላለ ጊዜ ወጪን ይቀንሳሉ።

👣2. ሲራመዱ ፍጥነት በተሞላበት ሁኔታ ይራመዱ (Walk faster)።
አንድ ሰው ስለ ራሱ ያለውን ስሜት ለማወቅ ብዙዎች ከሚጠቀሙባቸው ቀላል መንገዶች ውስጥ አንዱ አረማመዱን መመርመር ነው። ዝግ ብሎ የሚራመድ ነው? ሲራመድ ድካም ይታይበታል? ወይስ ሃይል የተሞላ እና አላማ ያለው አካሄድ አለው? በራሳቸው የሚተማመኑ ሰዎች በፍጥነት ይራመዳሉ። አፋጣኝ የሆነ ጉዳይ ባይኖርብዎትም እንኳ ፈጠን ብለው በመራመድ የራስዎን መተማመን ከፍ ማድረግ ይችላሉ።

👣3. ሁሌም ጥሩ የሰውነት አቋም ያሳዩ (Have a good posture)።
በተመሳሳይ መንገድ፣ አንድ ሰው ሰውነቱን የተሸከመበት መንገድ ሰውየው ስላለው የራስ መተማመን ብዙ ይናግራል። የተጣበቁ ትከሻዎች እና የተልፈሰፈሰ እንቅስቃሴ የሚያሳዩ ሰዎች የራስ መተማመን ማጣትን ያሳያሉ። እራሳቸውን ከፍ አድርገው አይመለከቱትም። ጥሩ አቋም በማሳየት ግን በራስ መተማመን ይሰማዎታል። ቀጥ ያለ ሰውነት ይኑርዎ፣ ጭንቅላትዎን ወደላይ ከፍ ያርጉ፣ ከሌሎች ጋር ሲነጋገሩ የዓይን ለአይን ግንኙነት ያድርጉ። ይህንም ሲያደርጉ ሌሎች ላይ አዎንታዊ ስሜት ያሳድራሉ፣ እናም በፍጥነት የበለጠ ንቃት እና ኃይል ያሰማዎታል።

👣4. ለራስዎ ስለ ራስዎ ማስታዎቂያ ይስሩ (Do personal commercial)
ጠንካራ ጎኖችዎን እና ግቦችዎን የሚያጎሉ ከ 30-60 ሰከንድ የሚዎስዱ ንግግር ይጻፉ። ከዚያም በራስ የመተማመን ስሜት በሚፈልጉበት ጊዜ በመስታወት ፊት ለፊት በመቆም (ወይም ጭንቅላትዎ ውስጥ በማነብነብ) ለራስዎ ይንገሩ።

👣5. በምስጋና የተሞሉ ይሁኑ (Have gratitude)
ምስጋና ሊሰማዎት የሚያነሳሳዎትን ነገሮች ሁሉ በአዕምሮዎ ውስጥ በመዘርዘር የሚያስቡበት ጊዜ በየዕለቱ ይመድቡ። ያለፉትን ስኬቶችዎን፣ ልዩ ችሎታዎችዎን፣ ወዳጆችዎን እና አዎንታዊ እንቅስቃሴዎን ያስታውሱ። ምን ያህል እርቀት እንደመጡም ለመገንዘብ ይረዳዎታል፣ ወደ ቀጣዩ ደረጃ ወደ ስኬት ለመሄድም በእጅጉ ያነሳሳዎታል።

👣6. ለሌሎች ሰዎች ስለ ጥሩ ስራቸው አድናቆትን ይለግሱ (Complement others)።
ስለራሳችን አሉታዊ በሆነ መልኩ ስናስብ፣ ብዙውን ጊዜ ሌሎችን ማጣጣል እና በጀርባቸው ላይ መጥፎ ነገር መሸረብ ላይ ትኩረት እናደርጋለን። ይህንን የኑሮ ዘይቤ ለማቋረጥ ሌሎች ሰዎችን የማመስገን ልማድ ይኑርዎት። ከሰዎች ጀርባ መጥፎ ነገር መመኘት ወይም መጠንሰስን አስወግደው በሰሯቸው ጥሩ ስራዎች አድናቆትን ለመግለፅ ይሞክሩ። በሂደቱ ውስጥም በጣም ይወደዳሉ፣ በዚህም በራስ መተማመን ይገነባሉ ። በሌሎች ውስጥ ምርጡን በመፈለግና በመመስከር በተዘዋዋሪ ምርጡን ወደ ራስዎ ዘንድም ያመጣሉ።

👣7. ከፊት ረድፍ ይቀመጡ (Sit in the front row)
ትምህርት ቤቶች ውስጥ፣ ጽ / ቤቶች እና ህዝባዊ ስብሰባዎች ላይ ብዙ ሰዎች መጨረሻ ለመቀመጥ ይጥራሉ። ምክንያቱም በቀላሉ መታየቱ ያስፈራቸዋል። ይህም በራስ መተማመን ማጣትን ያሳያል። በፊተኛው ረድፍ ላይ ለመቀመጥ ሲዎስኑ ይህንን ያለፈቃድ የሚመጣ ፍርሃት አሸንፈው በራስ መተማመንዎን መገንባት ይችላሉ። በተጨማሪም ከዋናው ፊት ለፊት ለሚነጋገሩ ሰዎች በይበልጥ ግልጽ ይሆናሉ።

👣8. ሃሳብዎን ይግለፁ (Speak up)
በቡድን ውይይቶች ወይም ብዙ ሰው በተሰበሰበበት ሁኔታ ውስጥ ብዙ ሰዎች ሃሳባቸውን ከመግለፅ ይቆጠባሉ። ምክንያቱም ሰዎች ከንግግራቸው ተነስተው እንዳይገምቷቸው ስለሚፈሩ ነው። ይህ ፍርሃት ትክክል አይደለም። ብዙ ጊዜ ሰዎች ከምናስበው ይልቅ የሰውን ሃሳብ የመቀበል ፍላጎት አላቸው። በእርግጥ ብዙ ሰዎች በተመሳሳይ ፍራቻ የተጠቁ ናቸው። በእያንዳንዱ የቡድን ውይይት ቢያንስ አንድ ጊዜ ለመናገር ጥረት በማድረግ የተሻለ የህዝብ ንግግር ክህሎት እንዲያዳብሩ ፣ ይበልጥ በራስ መተማመን እንዲኖርዎት እና በእኩዮችዎ ዘንድ መሪነትን እና ተቀባይነትን እንዲያገኙ ያደርግዎታል።

👣9. ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ልምድዎ ይሁን (Work out)
ልክ እንደ አለባበስ አይነት፣ አካላዊ ብቃት በራስ መተማመን ዘንድ ከፍተኛ ሚና አለው። ቅርጽዎ እንደተበላሸ ከተሰማዎት በሌሎች ዘንድ ዝቅ ተደርጎ የመታየት እና ሌሎችን መማረክ አለመቻል ስሜት ይሰማዎታል። አካላዊ እንቅስቃሴን በማድረግ አካላዊ ገጽታዎን ያሻሽላሉ፣ ኃይልን ያገኛሉ፣ ለአዎንታዊ ስራም ይነሳሳሉ።

👣10. የሚያደርጉት አስተዋፅዎ ላይ ያተኩሩ (Focus on contribution)
ብዙውን ጊዜ እኛ ስለምንፈልጋቸው ነገሮች እንጂ የሌሎች ሰዎች ፍላጎቶች እና በሌሎች ላይ ስለሚመጣው ጥሩ ለውጥ አናስብም። ስለራስዎ ማሰብ ካቆሙ እና ለተቀረው ዓለም ላይ ለውጥ እንዲመጣ በሚያደርጉት አስተዋፅኦ (መዋጮ) ላይ ካተኮሩ፣ ያሉብዎት ጉድለቶች አያስጨንቁዎትም። ይህ በራስ መተማመንን ይጨምራል እናም በከፍተኛ ተነሳሽነት እና ውጤታማነት እንዲሳተፉ ያስችልዎታል። ለዓለም ጥሩ እያደረጉ በሄዱ መጠን የግል ስኬት እና እውቅናንም እየተጎናፀፉ ይሄዳሉ።
ማስታወቂያ

ለተመራቂ ተማሪዎች

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎችን ከህዳር 24-27/13 ዓ.ም ወደ ግቢ እንዲገቡ ጥሪ ያደረገ ሲሆን ከዚህ ጋር ተያይዞ የ4ኛና የ5ኛ ዓመት የህክምናና የ4ኛ ዓመት የህግ ተማሪዎች ከተመራቂ ተማሪዎች ጋር የምትገቡ ይሆናል፡፡ ትምህርት ሰኞ ህዳር 28/013 ዓ.ም የሚጀመር መሆኑን ተገንዝባችሁ በጊዜ እንድትገቡ እናሳስባለን፡፡

መልካም መንገድ፡፡

@amuSUinfo
በወጣትነት ያለችህ አንዲት ሰዓት በእርጅና ዘመንህ ከሚኖርህ አንድ ቀን ጋር ይስተካከላል ። የወጣትነት እድሜ የህይወትህ ወርቃማው እድል ነው። በማይጠቅሙ ስራዎች አታባክነው።
አስብ፤ አስምር፤ ስራ!!
በወጣትነትህ ያሽኮረመምካት ህይወት በጉልማስናህ ለመዳራት ፣ በወጣትነትህ ያስፈገግካትን ህይወት በጉልምስናህ ለማስገልፈጥ ተአምር አትሻም ፡፡ የህይወት ፅጌዋ የሚፈነዳው ፣ ምንጯ የሚንፎለፎለው በወጣትነትህ ላይ ነው ፡፡ወጣት ከሆንክ የቀጠፍከው የጽጌረዳ እንቡጥ እጅህ ላይ ሊፈካ ይችላል ፡፡

ወጣት ከሆንክ ልትተክለው ያዘጋጀኸውን የብርቱካን ችግኝ የበሰለ ፍሬ ልትበላ ትችላለህ ፡፡ በቃ !! ወጣት ከሆንክ አለም አይገዛህም ፤ ትገዛዋለህ ፡፡ ህይወት አይበይንብህም ፤ ትበይነዋለህ ፤ ዘመን አይቃኝህም ፤ ትቃኘዋለህ ፡፡ ታድያ ይህ ሁሉ የሚሆነው የወጣት ልብ ከታደልክ ነው ፡፡

ወጣትነት ግጥምና ዜማ የለውም !

በግ ያጨባበጠን ዛሬያችን ፤
በማይገናኝ ትናንትና ፣
የኀሊት እየተሳበ ፣
ጎህ የቀደደው ነጋችን ፣
ምን ሊያመጣብኝ እንዳሰበ አላውቅም ፡፡

የወጣት ልብ ድርና ማጉ ጉጉትና ፍቅር ነው ፡፡ ጉጉትና ፍቅር ተዋህደው የሚፈጥሩት ብርሃን ነው ወጣትነት ፡፡ ወጣትነት በምትጠልቅ ጀምበር ተቅላሎት እንደተዋበ አድማስ ሟች ውበት ሳይሆን ፣ ገና ከአድማስ ማህጸን መውጣት የጀመረች የንጋት ጀምበር የምትነድፈው ብርሃን ነው ፡፡

በንጋት ብርሃን አለም ሁልጊዜ አዲስ ናት ፣ ህይወትም እንዲሁ ናት ፡፡ በወጣት ከሆንክ ያገጠጠብህ መከራ መሮ ጥርሱ ሳይሆን ፣ ለስላሳው ከንፈሩ ቀድሞ ይታይሀል ፡፡ ሊግጥህ ባሰፈሰፈው የመከራ ጥርስ በፍርሃት ለመራመድ ጊዜ የለህም ፤ በከንፈሮቹ ልስላሴ ውበት ተመደህ ፣ ተመስጠህ ትፈላሰፋለህ ፡፡አባትህ ሙሾ ለሚደረድርለት መከራ አንተ ለአዝማሪ ግጥምም ታቀብላለህ ፡፡

የልጅነት ጥሪትህን አሟጠህ ፣ የነፍስህን መሻት ናኝተህ የህይትህን ዘፈን ዜማና ግጥም የምትደርሰው አንተው ነህ ፡፡ አለም ታጅብሃለች ፡፡ በወጣትነትህ የሙሾ ግጥም ከተቀኘህ አለም የእድር ጡሩንባ አይገዳትም ፡፡ ለ<<አባ አየሽ ወይ ለምለም >> እርግጫ መንቀል ፤ <<ለሆያሆዬህ>> ምድርን በዱላ ነርታ አዋራ ማጨስ አይከብዳትም ፡፡ ለዚህ ደግሞ ከዚህ ከታጨቅንበት ድንኳን የተሻለ መሟገቻ አይገኝም ፡፡
((( ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ )))
Forwarded from ወጣቱ ና ሙዱ
ጠቃሚ ምክር ለሴቶች

እኔና ባሌ አራት አመታትን በፍቅር ኖራናል በትዳር ደግሞ 4 አመታትን ትዳርና ፍቅር የተለያየ ነው እያልኩ አይደለም እኔና ባሌ ከትዳር በሓላ ጥሩ የፍቅር ህይወት አልነበረንም ለዛ ነው ባሌ በጣም ዝምታኛ ነው ምንም ነገር አጥፊቼ ብሆን አይቶ ዝም ይላል ። ስለዚህ የበላይነት ይሰመኝ ጀመረ ጓደኞቼም ጀግና እንደሆንኩ መሰከሩ ታዲያ ኩራቴ የበለጠ ጨመረ ለባሌ ምንም አይነት ክቡር መስጠት አቆምኩ ። የትም ውዬ ማታ ላይ እመጣለሁ ባሌ በጣም ተናዶ እንኩዋን ዝም ይላል ። ታዲያ አንድ ቀን አምሽቼ ወደ ቤት ስመጣ በጣም ተናዶ ቆይ ለምን ለትዳርሽ ክቡር አይኖርሽም የድሮ ፍቅረችን ወዴት ሄደ አለኝ እኔ ንቄ ገፍቼ ሊገባ ስል በጥፊ መታኝ ለመጀመሪያ ጊዜ በጥፊ መታኝ ለመጀመርያ ጊዜ በኔ ላይ በር ቆልፎ እሱ ቤት አደራ ጥዋት ላይ ቤተሰቦቼ መጥቶ ፖሊስ አምጥቶ እሱን እስር ቤት ወሰዱት ከዛም ከእስር ቤት አስወጥቼ የፍቺ ጥያቄ አቀረብኩ ሁሉም ሰው ትክክል ነሽ አሉ ጓደኞቼም ጥሩ አደረግሽ የት አባቱ አሉኝ ።

ከዛ እሱም በሀዘን ተሞልቶ ድርሻዬን ሰጥቶ ብቻውን ተቀመጠ ። ከሁለት ዓመት በሓላ እሱ ሌላ ሚስት አግብቶ ልጆች ወልዶ ጥሩ ህይወት እየኖረ ነው ። የኔ ህይወት ግን ተበላሸ ። ትላንት ትክክል ነሽ ያሉት ሁሉ ዛሬ ትክክል አይደለሽም አሉኝ ። ትላንት የት አባቱ ወንድ የት ጠፍቶ የሉት እነሱ ለእራሳቸው ጥሩ ህይወት እየኖሩ ነው እኔ ግን ብቻዬን ቀረሁ ትላንት ከአንቺ ጋር ነን ያሉት ሁሉ ዛሬ ከኔ ጋር የሉም እህቶቼ ሴት ልጅ በተፈጥሮ ጠቢቡ ናት የተበላሽ ትዳር ማስተካከል ትችላለች ።

ስለዚህ በትዳረችሁ ባልሽ ሞኝ ብሆን እንኩዋን አንቺ ትዳረሽን ማስተካከል ትችያለሽ በትዳር መቀልድ ግን ትልቅ አለማውቅ ነው ። ከምንም በላይ ለትዳረችሁ ክቡር ስጡ ትዳር የሴት ልጅ ውበት ነው ። በትዳረችሁ መከላከል ለሚገባ ሰው እሱ ሰው መልካም አይደለም ። ስለዚህ ከእንደዚህ አይነት ሰው እራቁ ምክሩንም አትስሙ ።
ቴሌግራምን ለመታወቅ ሳይሆን ያወቅነውን ለማሳወቅ እንጠቀም ፡፡

ማወቅ መልካም ነው ያወቁትን ማሳወቅ ደግሞ ፍፁም በጎነት ነው ፡፡ በምድር ላይ የምናደርጋቸው መልካም ነገሮች ሁሉ በሰማይ ላይ የዘላለም ደመወዝ ሆነው ይከፈሉናል ፡፡ ሁሌም ቢሆን ከክፋት ይልቅ በጎ በጎውን ነገር እናስብ መልካምነት ለራስ ነውና ፡፡

ስለዚህ አንተም ይህ አሁን ያነበብከው መጣጥፍ ትምህርት ሰጪ ሆኖ ካገኘሀው የእርስዎ ዘመዶችህ እንዲያነቡትና ትምህርት እንዲወስዱ ዘንድ ሼር ያድርጉላቸው ።
ፌስቡክ ላይ በመጻፍ፣ በመዋጋትና በማዋጋት ነጻነታችንን መጠበቅ አንችልም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
**

“ፌስቡክ ላይ በመጻፍ፣ በመዋጋትና በማዋጋት ነጻነታችንን መጠበቅ አንችልም” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰላም ሚኒስቴር የመጀመሪያ ዙር የበጎ ፈቃድ የማኅበረሰብ አገልግሎት ስልጠና የወሰዱ ከ10 ሺህ በላይ ወጣቶችን በወዳጅነት ፓርክ በይፋ መርቀዋል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፤ በአባቶች ደምና አጥንት በነጻነት በቆመች አገር ላይ መሆናችንን መገንዘብና የትናንትን ጠቃሚ ነገር ማስቀጠልን ማስታወስ ያስፈልጋል።

ወጣቱ የተቀበለውን ነገር እንዳለ ማቆየት ሳይሆን ማሻሻል እንዳለበት ገልጸዋል።

ለአብነትም የወዳጅነት ፓርክ ላይ የተደረጉ ማሻሻያዎች አንስተው፤ ኢትዮጵያን ያቆዩ አባቶች ስራዎች ሳይዘነጉ ይበልጥ ማሻሻል፣ ማላቅና ማበልጸግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ማረም፣ ማበልጸግና ማላቅን ወጣቱ በልቦናው ማቆየት እንዳለበት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከግራ፣ ከቀኝ፣ ከኋላና ከፊት ለመገመት በሚያዳግት ደረጃ ትልቁም ትንሹም ተረባርቦ የተናሳባት ጊዜ ላይ ትገኛለች” ብለዋል።

የዚህ የውሸት ፕሮፓጋንዳና ጥላቻ ንግግር ዋና ዓላማ ከምዕተ ዓመት በፊት አልገዛም በማለት ለጥቁር ህዝቦች የነጻነት ተምሳሌት መሆኗን ዛሬም በድህነት ላይ ለመድገም መነሳሳቷ እንደሆነ ገልጸዋል።

“ኢትዮጵያ ድህነት አያስፈልገኝም ብልጽግናን እሻለሁ፤ መለመን አልፈልግም መስጠትን እመኛለሁ እያለች ነውና ይህችን አገር ካላቆምናትና ካልቀጨናት በስተቀር አሁንም ለጥቁር ህዝቦች አረአያ ትሆናለች የሚል ስጋት በሰፊው ይናፈሳል” ብለዋል።

ትልቅ ትንሹ ቢጮህና ብዙ ውሸት ቢነገር ለጥቁር ህዝቦች ነጻነቷን ጠብቃ አረአያ የሆነችው ኢትዮጵያ ዛሬም በልጆቿ ጥረትና ትብብር ታግዛ የብልጽግና ምሳሌ እንደምትሆን ተናግረዋል።

“ጆሯችሁን፣ ልባችሁን፣ አዕምሯችሁን ጠብቃችሁ ኢትዮጵያን ማላቅ፣ ማበልጸግ፣ መውደድና በክብር መስዋዕት መሆን የኩራት ሁሉ ምንጭ እንደሆነ አውቃችሁ እንድታገለግሉ፣ እንድትጠብቋት፣ እንድታሻግሯት፣ ለሚመጡ ወጣቶች ተስፋ ለአዛውንቶች ደግሞ እንድትሆኑ አደራ” ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የአገር መከላከያ ሰራዊትና የፌዴራል ፖሊስ ብዙ ወጣቶች እንዲቀላቀሏቸው እንደሚፈልጉ ገልጸው፤ ከቅርብና ከሩቅ ብዙ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚፈልጉ ሃይሎች ስላሉ መጠናከር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

ብዙ ወጣቶች በሰራዊት ውስጥ ተቀላቅለው ከማገልገል ይልቅ በፌስቡክ እንደሚዋጉና እንደሚያዋጉ ገልጸው፤ “በፌስቡክ ነጻነታችንን መጠበቅ አንችልም፤ ዋጋ ከፍለን ራሳችንን ካልሰጠን በስተቀር በያላችሁበት በምትናገሩትና በምትጽፉት የኢትዮጵያን ህልውና ማስጠበቅ ስለማይቻል በመከላከያና በፖሊስ ሰራዊት ውስጥ ተሳትፈን አገራችንን መጠበቅና ህልውናዋን የሚገዳደሩ ሃይሎች የማይችሉ መሆኑን ማሳየት ያስፈልጋል” ብለዋል።
Forwarded from O
Ethiopian Airlines [For Fresh Graduate]

Ethiopian Airlines Group would like to invite qualified candidates for the following position.

1:- Trainee Pilot/Trainee Pilot Instructor
2:- IATA FOUNDATION FOR TRAVEL & TOURISM
3:- LINE & HANGAR MAINTENANCE
4:- PLASMA & WELDING TECHNICIAN
5:- STRUCTURE MAINTENANCE TECHINICIAN
6:- AVIONICS MAINTENANCE TECHNICIAN
7:- AIRCRAFT PAINTER
8:- CABIN MAINTENANCE TECHINICIAN
9:-AIRCRAFT MECHANICAL COMPONENT MAINTENANCE
10:- COMMERCIAL AND GROUND SERVICES TRAINEE

📌ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ👇👇
👉See Detail:- https://bit.ly/37QJc8o


Please Don't forget to share/ወዳጅ ዘመድዎ እንዲደርሰው ሼር ያድርጉ

-------//--------

ሌሎችን የሥራ ማስታወቂያ መረጃዎችን ለመከታተል
🔰follow us for more Job Notification on ➘➘➘

Facebook:-
www.facebook.com/HarmeeJobs

Telegram :-
https://hottg.com/BeeksisaaHojii

website:-
www.harmeejobs.com
እንኳን ደስ አለን!

ከ8 ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ወደ አፍሪካ ዋንጫ ተመልሷል!

#እግር_ኳስ #የኢትዮጵያ_እግር_ኳስ_ብሔራዊ_ቡድን #ዋልያዎቹ #Ethiopia
Forwarded from HaHuJobs
#በነፃ የሶፍትዌር ኢንጅነር ይሁኑ

Alxethiopia ያዘጋጀው ልዮ የ12 ወር የሶፍትዌር ኢንጅነሪግ ስልጠና ተሳታፊ ይሁኑ ። ስልጠናው የሚሰጠው በበይነ መረብ ያለምንም ክፍያ ሲሆን ለስልጠናው ብቁ ለመሆን የሚሰጡ ምዘናዎችን ማለፍ ያስፈልጋል ። ለስልጠናው ለመመዝገብ በኢሜል አድራሻዎ ከታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪ ላይ ያመልክቱ።

Be a Software Engineer for #FREE

Register for Alxethiopia's 12-month software engineering training. The training is provided online free of charge and only requires submission of assessments to qualify for the program . To apply please follow the link below which only requires you to have an email address.

ይህንን #የነፃ ዕድል ለሌሎችም በማጋራት ተጠቃሚ ያድርጎቸው ።

እዚህ ገፅ ላይ መመዝገብ ይችላሉ
alxethiopia.com/software

#ሼር #SHARE

@hahujobs @hahujobs_bot
እንኳን ለበዓለ ስቅለት አደረሳችሁ!!!


ክርስትና ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር መሰቀልን ይጠይቃል። በሞቱ ማኅበርተኛ ስንኾን በትንሣኤውም እንኾናለን። ሥጋችንን ካልሰቀልን ሥጋችን ይነዳናል። በሥጋ አገዛዝ የምንፈራፈረው አብረን መሰቀል አቅቶን ነው። ስንሰቀል ፈቃደ ነፍስ በልዩ ኃይል ትለመልማለች። ከመስቀሉ ርቀን መሰቀሉንም ፈርተን ክርስቶሳዊ መኾን አንችልም።


ዕለተ ዐርብ አይሁድ እና ሮማውያን የሰቀሉት የመሰላቸው በዙፋነ መስቀል የነገሠባት ናት። በዚህ ዙፋን ላይ የተሰጠውን የምሕረት ፍርድ የመሰለ አይገኝም። መሰቀልህ ቢያስለቅሰንም ለጥቅማችን አድርገህልናልና ለዘለዓለም እናመሰግንሃለን።
እንኳን ለጌታችን ለአምላካችን ብርሃነ ትንሣኤ አደረሳችሁ !

ስለ ሰው ልጆች ፍቅር ጌታችን ሁሉን የትሕትና ሥራ ፈጽሟል። ወድዶ ፈቅዶ የትሕትናን ሥራ ለመናገር በሚያዳግተን ደረጃ ዝቅ ብሎ በመፈጸሙ ኃይሉ አልታየም ነበር። ይህም መኾኑ ብዙዎች በግርታ ተሳስረው እንዲቀሩ አድርጓቸዋል። እስከ ሞት ያውም የሰዎች የጭካኔ ዐቅም እስከማይከደን ድረስ።


በትንሣኤው ግን ክንደ ብርቱው ሞትም፣ የተወቀረ ዐለት፣ የተገጠመ ድንጋይ፣ የታተመ ማኅተም፣ የፈረጠመ ጡንቻ ይህ ሁሉ ቢነባበርም ሊያስቀረው የቻለ አንዳችም አልነበረም። ዲያብሎስም ከተዋናይነት ወደ ተመልካቺነት ተዋረደ። ከሚመለከት በቀር ዙፋኑን በዘረጋባት ሲኦልም ማዘዝ አልተቻለውም። ቁጭ ብሎ ከመመልከት በቀር ስፍራ አላገኘም።

"እግዚአብሔር ይነሣ፥ ጠላቶቹም ይበተኑ" እንዲል። መዝ ፷፯ ፡ ፩።

"እሳት ጭራሮውን እንደሚያቃጥል፥ እሳትም ውኃውን እንደሚያፈላ፥ ስምህ ለጠላቶችህ ይገለጥ ዘንድ፥ አሕዛብም በፊትህ ይንቀጠቀጡ ዘንድ" ተብሎ እንደተነገረ የትንሣኤው ኃይል ሊነገር አይቻልም። ኢሳ ፷፬ ፡ ፪።
🌿ከ Life ብዙ ተምሬያለሁ!


⚜️. አንዳንድ ሰው እንዲያፈቅራችሁ ማድረግ እንደማይቻል ተምሬያለሁ ፤ ማድረግ የሚቻለው ጥሩ አፍቃሪ መሆን ብቻ ነው ።

⚜️.ብስለት የሚመጣው ከሚያጋጥሙን ተሞክሮዎች ዓይነትና ከተሞክሮዎቹ ከቀሰምናቸው ትምህርቶች እንጅ ካከበርናቸው የልደት በዓሎች ብዛት እንዳልሆነ ተምሬያለሁ ።

⚜️.እንዳንዴ የቱንም ያህል ለሌሎች ብጨነቅ እና ግድ ብሰጥ አንዳንዴ አንዳንዶች በመልሱ ግድ ላይሰጡ እንደሚችሉ ተምሬያለሁ ።

⚜️.ቤተሰብ ሁልጊዜም መከታ ድጋፍ እንደማይሆን ተምሬያለሁ ። ጓደኞች ምንም ያህል ጥሩ ቢሆን አልፎ አልፎ ማስቀየማቸው እንደማይቀር ተምሬያለሁ ። ባስቀየምናቸው ሰዎች ይቅር መባል በቂ ያለመሆኑንና ራስንም ይቅር ማለትም እንደሚያስፈልግ ተምርያለሁ ።

⚜️.መታመንን ለመግንባት ዘመናት እንደሚያስፈልግ ፤ ለማውደም ግን ሰከንዶች ብቻ እንደሚበቁ ተምሬያለሁ ።

⚜️.አንዳንድ ጊዜ ተንሸራትተህ ስትወድቅ ይረጋግጡኛል ብለህ የምትጠብቃቸውና የምትፈራቸው ሰዎች ብድግ አድርግው በማንሳት እንደሚያስገርሙህ ተምሬያለሁ ።

⚜️.እውነተኛ ጓደኝነት እንደዚህም እውነተኛ ፍቅር በቦታ ርቀት ሳይግደብ ማበብ መፍካቱ እንደማይቆም ተምሬያለሁ ።

⚜️.በአስተዋይነት "እምቢ" ማለት ሁልጊዜም የንፉግነት ምልክት ያለመሆኑን “እሺ” ማለትም ሁልጊዜ ምግባረ ሰናይነትን እንደማያሳይ ተገንዝቢያለሁ ።

⚜️.ራስን ከጥፋተኝነት ስሜት እንዲሁም ከጥላቻ የምንገላገልበት ብቸኛ መንገድም የአለፈውን ጊዜ ረስተን ከአሁን ጋር እርቅ ማድረግ ስንጀምር እንደሆነ ተምርያለው ።

📚የአልኬሚስት
ደራሲ ፖውሎ ኩዌልሆ

ነገ መልካም ይሆናል !
እንኳን አደረሳችሁ !

ለመላው እስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1442ኛው ለኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሰን ፤ አደረሳችሁ። ዒድ ሙባረክ !

በዓሉ የሰላም ፣ የአንድነት ፣ የፍቅር እንዲሁም የመተሳሰብ ይሆንልን ዘንድ እንመኛለን።

በዓሉን ስታከብሩ የተቸገሩት ፣ ያጡትን ፣ በሰላም እጦት የሚሰቃዩትን ፣ በሰላም እጦት ወገን ዘመዶቻቸውን ከጎናቸው የተነጠቁትን ፣ ከሞቀው ቄያቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ የቀሩትን ወገኖቻችን በማሰብ ይሆን ዘንድ አደራ እንላለን።

ውድ ቤተሰቦቻችን በበዓሉ ወቅት አስፈላጊው የኮቪድ-19 ጥንቃቄ ማድረግ እንዳትዘነጉ።

ሀገራችንን ፈጣሪ ይጠብቅልን!!
የሰውን ልጆች ሁሉ በሰላም ያኑርልን!!
መልካም በዓል !
#ይነበብ

#የህይወት_ጎበዝ_ሁን!

ከክፍል አንደኛ መውጣትህ፣ ሰቃይ ተማሪ መሆንህ፣ በማዕረግ መጨረስህ- በህይወትህ ስኬታማ እንድትሆን ዋስትና ይሆንሃል ማለት አይደለም። በኢኮኖሚክስ በማዕረግ ልትመረቅ ትችል ይሆናል፣ ይሁንና ከሁሉ የተሻለ ገቢ ታገኛለህ ማለት አይደለም። ጎበዝ የህግ ተማሪ ነበርክ ማለት ጎበዝ ጠበቃ ትሆናለህ ማለትም አይደለም። ይሀውልህ፤ ህይወት- ፅንሰ ሃሳብን (concept) ከመረዳት፣ ነገሮችን ከማስታወስ (Memoriase ize)ና፣ ፈተና ላይ ከመተግበር (reproduce) በላይ አቅም ትፈልጋለች።
• ትምህርት ቤቶች፣ ሰዎችን 'ለማስታወስ ችሎታቸው' ዕውቅና ሲሰጡ፤ ህይወት ግን፣ ሰዎችን 'ለተግባራቸው' ዕውቅና ትሰጣለች።
• ትምህርት ቤቶች ማስጠንቀቂያ (caution) ሲሰጡ፤ ህይወት ግን ድፍረትን ትሰጣለች።
• ትምህርት ቤቶች በ"ደንብ" የሚኖሩትን ሲያመሰግኑ፤ ህይወት ግን ደንብን ጥሰው፣ አዲስ ህግን ያስቀመጡትን ታወድሳለች።
ታዲያ ሰዎች በትምህርት ቤት ጠንክረው መማር የለባቸውም እያልኩ ነው?- በፍፁም። መማርህ የግድ ነው። ይሁንና "አንደኛ" ለመውጣት ብለህ ሌሎች ነገሮችን ሁሉ መስዋእት አታድርግ እያልኩህ ነው።
ያንተ ጉብዝና በ10ኛ ክፍል ውጤት አዘለለህ፣ በ12ኛ ክፍል ውጤት አስፈነደቀህ፣ በከፍተኛ ትምህርት ውጤትህ አስወደሰህ...ከዛስ? - ከዛማ ቅጥረኛ ሆነሃል። የወር ደሞዝ ትጠብቃለህ፣ ፍቃድህ በአለቃህ (ሰቃይ ተማሪ ባልነበረው) ላይ ወድቋል።
ትላንት ግብረገብ ላይ ጥሩ ሆኖ በሌላ ዘርፍ ግን ደክሞ የናቅከው ተማሪ፣ ዛሬ የሞራል አለቃህ (የሃይማኖት ሰው) ሆኖ ይመራሃል፤
ትላንት ስነ-ዜጋ ላይ በርትቶ በሌላው ግን ደክሞ የተቸኸው ተማሪ፣ ዛሬ ባለስልጣን ሆኖ አጠገቡ ለመድረስ የምትናፍቀው ሰው ሆኗል፤
ትላንት ስእልና ሙዚቃ ላይ ጊዜውን እያጠፋ በሌላው ግን ስለደከመ የናቅከው ተማሪ፣ ዛሬ የምታደንቀው አርቲስት ነው፤
ትላንት ሽቦ ሲወጥር፣ እንጨት ሲቆርጥ- ከነጓደኞችህ ያሾፍክበት ተማሪ፣ ዛሬ እርሱ ጋር ለመቀጠር በብርቱ የምትፈልገው የትልቅ ኢንዱስትሪ ባለቤት ሆኗል።
የትምህርቱ ጎበዝ በህይወት ጎበዞች ተበልጠሃል። ዛሬ ላይ ቆመህ የነርሱን ህይወት ትናፍቃለህ። ደስታህ በደስታቸው፣ ሀዘንህ በሀዘናቸው ላይ ተመሥርቷል። አሁንም ግን ጊዜው አልረፈደም። እስትንፋስህ እስካለች ህይወት ትቀጥላለች። ራስህን በክፍል አትገድበው፤ በምግባርህ ጎልተህ ውጣ፤ የመሪነቱንም ድርሻ ውሰድ።
እስቲ የንግድ ሥራ ጀምርና አይሳካልህ፣ ብዙ አማራጮችን ትቀስምበታለህ። ለምርጫ ተወዳደርና ተሸነፍ፣ የፓለቲካ ሳይንቲስት የማያስተምርህን ነገር ያስተምርሃል። ውስጥህ ያለውን ተሰጥኦ አውጣውና ይታይ፣ አጎልብተውም፤ በሙያህ ዘርፍ ብቻ ሳትገደብ መፅሐፍትን አንብብ፣ ያመንክበትን ነገርም አድርግ። በቃ! ጎበዝ ተማሪ ለመሆን ከማሰብ ይልቅ፣ ጎበዝ ሰው ለመሆን አስብ። ትምህርት ቤትህን አለምህ አታድርገው፣ አለምህን ትምህርት ቤትህ እንጂ!። ልብ በል፤ ፈጣሪም የሚረዳው የሚሞክሩትን ነው። ከሰማይ ይልቅ በምድር ያስቀመጠህም በአላማ ነው። የምትበርበት ክንፍ ያልሰጠህ አውሮፕላን ሰርተህ እንድትበር፣ ተሽከርካሪ እግር ያላደለህ መኪና ሰርተህ እንድትሽከረከር ነው። ከርሱ ዘንድ፣ በየቀኑ የሚሰጥህን ዕድል ያለመሰሰት ተጠቀምበትና የህይወት ጎበዝ ሁን!
ስለዚህ አንድ ምክር ልምከራቹ በሰዎች ሳይሆን በራሳቹ ተመሩ። ምክንያቱም እናንተ ሰው እንጂ ወንዝ አደላችሁም። ግቢ ውስጥ በራሳችሁ ዛቢያ ተንቀሳቀሱ። ሌሎችን አታዳምጡ ማለቴ ግን አደለም። የህይወት መንገዳችሁን ራሳችሁ ምረጡ መክሊታችሁንም እንደዛው። በቀጣይ አመት የህይወታችሁን ወሳኝ ምዕራፍ ትወስናላችሁ። ማለትም የ ዲፓርትመንት ምርጫ። እዚክ ላይ እራሳችሁን እወቁ ምን መሆን እችላለሁ ምን ያስፈልገኛል የሚለውን ልባችሁን አዳምጡ። ግን ከሁሉም በላይ የህይወት ጎበዝ ሁኑ።


ብርሃኑ
▫️ህይወትህን የሚቆጣጠሩት ያመንክባቸው ሀሳብና እምነቶች ናቸው፤ እንደማትችል አምነህ ግን እስኪ ለማንኛውም ልሞክር ብለህ የምታደርጋቸው ነገሮች ሁሉ መጨረሻቸው ደካማ ውጤት ነው።

አየህ ምንም ነገር ላይ ለመስራት ከመነሳትህ በፊት ነገሮችን ሁሉ መወጣት እንደምትችል አምነህ መጀመር አለብህ፤ ያኔ በህይወትህ ሁሉን የመቻል አዲስ ምዕራፍ ትከፍታለህ! ፈጣሪ በሰጠህ አቅምና ፀጋ ማመን ጀምር ወዳጄ!



With HABTE(ትንሹ ፈላስፋ)
The Global Undergraduate Exchange Program (Global UGRAD) brings future leaders to the United States to experience U.S. higher education, gain critical professional skills, and explore new cultures and values.
sponsored by the U.S. Department of State with funding provided by the U.S. Government
😳Global UGRAD alumni go on to receive Fulbright grants, obtain prestigious international internships, and work in business and government in their home countries and regions.
https://www.worldlearning.org/program/global-undergraduate-exchange-program/

@youthkipper
GREAT OPPORTUNITY FOR GRADE 9 - 12 STUDENTS

Do you want to change the world? There is a $500,000 scholarship for you.

Eric Schmidt, the former CEO of Google, has committed $1 billion to equip brilliant youth with the resources and support needed to address humanity's most pressing problems.

The Rise scholarship program is the result. Each year, Rise selects 100 winners to receive a lifelong scholarship that includes up to $500,000 in scholarships (for university and beyond) as well as mentorship and access to career development opportunities.

You are eligible if you are born between July 2, 2004 and July 1, 2007. Rise uses a smartphone application to select students for this scholarship program.

Click this link (https://gethelloorg.page.link/wDwx) on a mobile device and download the HelloWorld application.

👉 Create a profile by 22 December.
ጥሮ አደር እንጂ አውርቶ አደር ምኞቱን አያሳካም!!
በከፈለኝ ዘለለው [ሐዋዝ]

ማዘናችን ለመደሰታችን ዋዜማ ነው፡፡ ሁሉም ነገር ጣፍጦ አልተሰጠንም፡፡ መኖርም ያልጣፈጠውን የማጣፈጥ ረጅምና አድካሚ ጉዞ ናት፡፡ የተፈጠርነው የሚያስቸግረንን ችግር አስቸግሮ ለመኖር ነው፡፡ ለችግራችን ተንበርካኪ ሳይሆን ችግሮቻችንን አንበርካኪ እንሁን!! እንዳዘራራችን አስተጫጨዳችን ይወሰናል፡፡ በመሆኑም … ለሕልማችን ሟች እንጂ ሕልማችንን አሟች አንሁን፡፡ ‘መሸመን ጀምር እግዜር ክሩን ይሰጥሀል ነውና በጣርነው ልክም ወደ ስኬት እንጠጋለን፡፡ መልፋት ካልቻልን መገፋታችን አይቀርም፡፡ ሕይወት የጎደለብንን ለመሙላት የምንሮጣት ሩጫ ናት።

እኔ … ሲያጥቡት የማይጠራ ዕድፍ እንዳለ አላምንም፡፡ ግና አጣቢውና አስተጣጠቡ ለዕድፉ መጥራትና አለመጥራት ወሳኞች ይሆናሉ፡፡ የሆነው ሆኖ ግን … ጥረት ከ … እስከ የሚባል ወሰን የለውም፡፡ ጥረታችን እስትንፋሳችን ስትቆም የሚቆም እንጂ በደከመንና በሰለቸን ቁጥር ከላያችን አውርደን የምንጥለው ወቅታዊ ሸክም አይደለም፡፡ ከሕይወት ምንጭ እስከ መኖር ጥግ ድረስ እየጣርን መኖር ይጠበቅብናል፡፡ ምንያቱም የምንደርሰው ስንራመድ ብቻ ነውና! ጣፋጭ ፍሬዎች በሙሉ መራራ መስዋዕትነትን ያስከፍላሉ፡፡ ሣር ካልሰጠናት ላም ወተትን ማግኘት ስለማይቻል ለውጣችንን ቁጭታችን ውስጥ ሳይሆን ሩጫችን ውስጥ እንፈልግ፡፡

በእርምጃችን ወቅት የሚያጋጥሙን ብዙ አስቸጋሪ ደመናዎች ይኖራሉ፡፡ ግና … መከራና ጉም እያደር እንደሚቀሉ እንመን፡፡ ተራምደን ደራሽ ለመሆን ጀምሮ ጨራሽ መሆን ያሻናል! እየለመለምን የምንረግፍ ሳይሆን እያበብን ፍሬ የምንሰጥ ዘሮች ለመሆን ራሳችንን የራሳችን አረም ከማድረግ እናቅብ፡፡ ስኬት የብዙ ውጣ ውረዶች ድምር ውጤት ናት፡፡ እናም የጣፈጠውን ለማጣጣም የመረረውን ቀምሶ ማለፍ አያስጠላን፡፡ ጠግቦ አዳሪ ለመሆን ለፍቶ ኗሪ መሆን የውድ ግዳችን ነው፡፡ ጥሮ አደር እንጂ አውርቶ አደር ምኞቱን አያሳካም፡፡ ሳይሰሩ እያፈሩ እንጂ እየኮሩ የኖሩ የሉም፡፡ በኩራት ለማምሸት በትጋት እንዋል፡፡ ያማረ ነገን ለመፍጠር የተዋበ ዛሬን መኖር እንቻል። አስቸጋሪ ችግሮች ወደ አስደሳች ነገሮች መሸጋገሪያ ድልድዮቻችን ናቸው፡፡ የምንኖረው ከችግሮች ነፃ በሆነች ምድር ላይ አይደለም፡፡ በመሆኑም ችግሮቻችንን የመሸሽ ሳይሆን ችግሮቻችንን የማሸሽ ሥራ እንስራ፡፡
HTML Embed Code:
2024/04/19 07:26:00
Back to Top