ያሬዳዊ ግጥም) ያሬድ ከበደ
መንቶ
*
ሼሁም ቆቡን ደፋ የእምነት አባት ቄሱም
መስቀሉን አንግቦ ሻሹን ሲጠመጥም
*
ሙስሊም ክርስትያኑ ፆማቸው ሲገጥም
**
ከመስጅዱ ቅጥር ከበተስኪያን አፀድ
አሀዱ ቅዳሴ ማልዶ ሲባል አዛን
****
የፍቅርን ማዕድ ተቋድሰን ባንድነት
አላህም እግዜር ነው የሚል ቃል ሲገዛን
**
የተሰቀለውን ህማሙን ለማሰብ
አርብ የሚሏት ግብዣ ስታቀጣጥረን
****
እንደየ እምነታችን ስንለማመነው
በፆም በስግደቱ ባንድነት አፍጥረን
*
ዱአ ፀሎታችን ካምላክ ዘንድ ቀርባ
ለልባችን መሻት ፍቅር አስተምራን
**
በዥንጉርጉር ዓለም
####
አንድ እውነት አግባብቶን
እኩል ይሰበካል ወንጌልና ቁራን
>>Click here to continue<<