TG Telegram Group & Channel
ዘ-ሐበሻ | United States America (US)
Create: Update:

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለትግራይ ክልል የ20 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገች
=======#=======

ሰኞ ሐምሌ 3 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጦርነቱ ወቅት ከፍተኛ ጉዳት ለደረሰበት የትግራይ ክልል ለሰብዓዊ ድጋፍ እና ለመልሶ ግንባታ የሚውል የ 20 ሚልየን ብር ድጋፍ አድርጓል።

በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የተመራውና የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የአገር ሽማግሌዎችና ልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊዎች ያሉት የሰላም ልዑክ፤ ይህንን ድጋፍ ለማስረከብ እና በትግራይ ክልል ከሚገኙ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ለመወያየት ወደ መቐለ ማቅናቱ ይታወቃል፡፡

ቅዱስነታቸው ልዑካኖቹን መርተው መቀሌ ዓለም ዓቀፍ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ፤ የትግራይ ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በክልል ትግራይ በጦርነት ለተፈናቀሉ ወገኖች የፈቀደውን ሃያ ሚሊዮን ብር የሰላም ልዑኩ ለክልሉ ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ አስረክቧል፡፡

በድጋፍ ርክክብ መርሐ ግብሩ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ፣ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ እና ልዑካን ቡድኑ ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለትግራይ ክልል የ20 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገች
=======#=======

ሰኞ ሐምሌ 3 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጦርነቱ ወቅት ከፍተኛ ጉዳት ለደረሰበት የትግራይ ክልል ለሰብዓዊ ድጋፍ እና ለመልሶ ግንባታ የሚውል የ 20 ሚልየን ብር ድጋፍ አድርጓል።

በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የተመራውና የብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የአገር ሽማግሌዎችና ልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊዎች ያሉት የሰላም ልዑክ፤ ይህንን ድጋፍ ለማስረከብ እና በትግራይ ክልል ከሚገኙ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ለመወያየት ወደ መቐለ ማቅናቱ ይታወቃል፡፡

ቅዱስነታቸው ልዑካኖቹን መርተው መቀሌ ዓለም ዓቀፍ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ፤ የትግራይ ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በክልል ትግራይ በጦርነት ለተፈናቀሉ ወገኖች የፈቀደውን ሃያ ሚሊዮን ብር የሰላም ልዑኩ ለክልሉ ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ አስረክቧል፡፡

በድጋፍ ርክክብ መርሐ ግብሩ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ፣ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ እና ልዑካን ቡድኑ ተገኝተዋል፡፡


>>Click here to continue<<

ዘ-ሐበሻ










Share with your best friend
VIEW MORE

United States America Popular Telegram Group (US)